tg-me.com/yenetube/54912
Last Update:
በህወሓት እና ሻዕቢያ መካከል የተፈጠረው ጥምረትና ግንኙነት በፌደራል መንግሥቱ መቋረጥ አለበት ሲሉ የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ!
በቅርቡ ህወሓትና ሻዕቢያ ጥመረት እየፈጠረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ የሁለቱ አካላት ጥምረት በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሊቋረጥ ይገባል ሲሉ የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አሳስበዋል፡፡የቀድሞዋ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም፤ "ይህንን ለጦርነት የተደረገ ጥምረት መንግሥት ሊያቋርጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አባልና ከፍተኛ አመራር እንዲሁም የዲሞክራሲ ስምረት ትግራይ ፖርቲ መስራች ውስጥ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ "የሁለቱ አካላት ጥምረት ዓላማ ግልፅ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሐትና የኤርትራ መንግሥት ጥምረት መፍጠር ለጦርነት ዓላማ የተደረገ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።
በተጨማሪም በትግርኛ "ፅምዶ" ወይንም "ጥምረት ለሀቀኛ ሰላም ለትግራይ እና ኤርትራ" በሚል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተደረገ መሆኑንም መመልከት ተችሏል።ይህንን ጥምረት በሚመለከት ሀሳባቸውን የሰጡት የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም "በግልፅ ለጦርነት የተደረገ ጥምረት ነው" ብለዋል።
"ሕዝብን ከተደቀነበት ጦርነት ማዳን ላይ መስራት አለብን" ያሉ ሲሆን፤ ጦርነቱ የማይቀር እንኳን ቢሆን ዱላው ሕዝብ ላይ እንዳያርፍ መስራት አለብን" ሲሉም ገልጸዋል።"አሁን ላይ በግልፅም ይሁን በድብቅ ጥምረቱ ይታያል" ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ "ይህንን ማስቆምና መቁረጥ ያለበት የትግራይ ሊሂቃንና ፌደራል መንግሥት ነው በማለት ሀሳባቸውን" ሰጥተዋል።
ሌላው ሀሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡት የቀድሞ የህወሕት አባልና ከፍተኛ አመራር ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፤ "በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ ከሌላ ሀገር ጋር ማን ግንኙነት መፍጠር እንዳለበት ይታወቃል" ብለዋል፡፡"ሕገ-ወጥ ግነኙነት ሲኖር ደግሞ ማስቆም ያለበት ማን እንደሆነም ግልፅ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።"ይሁን እንጂ ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት ያልጠራ ነው፤ ነገር ግን ግንኙነቱ በመርህ ላይ ካልተመሰረተ ትክክል አይለም" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል።
በዚህ ጥምረት ዙሪያ የፌደራል መንግሥት በግልፅ ያስታወቀው ነገር ባይኖርም፤ ባለፈው ሳምንት አርብ በትግራይ ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ የሚጠይቅ ወይይት ተካሂዶ ነበር።የፌደራል መንግሥት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከልን በመወከል የተገኙት አቶ መለሰ አለሙ፤ "የፌደራል መንግሥት ኃላፊነት እንዳለ ሆኖ የትግራይ ፖለቲከኞችም ለሰላም ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።"የድንበር ጉዳይን በተመለከተ መንግሥት ሉዓላዊነቱን በፍፁም አሳልፎ አይሰጥም" ያሉም ሲሆን፤ የውስጥ ችግሮች ከተፈቱ ሌላውን ማስተካከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
BY YeneTube
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/yenetube/54912