Telegram Group & Telegram Channel
📖የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መግቢያ📖
✞ክፍል አራት✞
🔐አጭር የጥናት መመሪያ🔐

መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ቋንቋ እንደ መጻፉ እግዚአብሔር የጸሐፊዎቹን ቋንቋ፣ ባህል፣ የሚኖሩበት አካባቢ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ፣ስነ ቃል ወዘተ ተጠቅሞ ስላፃፋቸው የመጽሐፉን ክፍል ስናጠና መጀመሪያ ስለፀሐፊው ማንነት ቀጥሎም የስነ ጽሑፉ ቅርፅ ባሕርይ(ዓይነት)፣ የሐገሩ ሰዋስው(አገባብ) ወዘተ መረዳት ያስፈልጋል።ለዛሬ በጥናት ጊዜ የሚጠቅሙን አንኳር ሐሳቦችን እንይ

1ኛ.መመልከት ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
ግምታዊ አሰተሳሰብ ሳንሰጥ እንዲሁም ከሌሎች ወይም በስብከት የሰማነውን ትርጉም ቶሎ ሰጥተን አንለፍ ይልቅ ጥቅሶቹ በደምብ ሐሳባቸውን መረዳት "የተባለውን ነገር እውነት ይገልፃሉ?"ብሎ ማንበብ እንጂ ትርጉም ለመስጠት አለመቸኮል።ጸሐፊው በዚህ ክፍል ምን ማለት እንደፈለገ አንብበን በጥሞና መረዳት። በሚከትሉት ጥያቄዎችም በመደገፍ እውነቱን ማስተዋል ይገባል
★ባለታሪኮቹ እነማን ናቸው? ምን ተሰራ ምንስ ተደረገ? የት ቦታ በምንስ ሁኔታ? መቼ? እንዴት? ለምንስ? ውጤቱስ ምን ነበር? ምንስ ተፈጠረ?
የምናጠናውን ክፍል ከአውደንባቡ ለይተን ማውጣት የለብንም!!

★2ኛ.መተርጎም ፦ምን ማለቱ ነው? የሚለውን በመጠየቅ ፍቺ መስጠት። በአሁኑ ጊዜስ ተመሳሳይ የሆነው ፍቺው ምንድነው? መዝገበ ቃላት በመጠቀም ቃላቶቹን ፣ ሐረጎቹን፣ ቅኔያዊ አነጋገሮችንና ዐረፍተ ነገሮችን መተንተን

★3ኛ.ማዛመድ
ለምን ይህንን ሃሳብ ፣ ሐረግ፣ ቃል ተጠቀመ? ለምንስ ይህንን እዚህ መጥቀስ አስፈለገው? ያሉት የተለያዩ ሃሳቦችስ እንዴት ይዛመዳሉ?
ጠቃሚውን ሃሳብ ማግኘት።
ጎልቶ የሚታየውን መንፈሳዊ ሃሳብ ወይም መልዕክት ለይተን ማውጣት።ከሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ጋረ መስማማቱን ማረጋገጥ።
ዋናውን መልዕክት ቸል ብለን በጥቃቅን ነገሮች ላይ እንዳናተኩር ያልገባንን ለሌላ ጊዜ ጥናት ማስተላለፍ ወይም ሌሎችን በመጠየቅ መረዳት።

★4ኛ.የተለያዩ ሊቃውንት ትንታኔዎችን መመልከት
የአንዱን ሊቅ ሐሳብ ብቻ በመያዝ ትርጉም ሰጥቶ አይታለፍም!! ምክንያቱም በሊቃውንቱ አፈታት ወይም አተናተን ላይ መራቀቅ ሊኖር ይችላል ማለትም የአውደንባቡ ሐሳብ ሌላ ሊሆን ይችላል ነገር ግን በመራቀቅ እንዲህ ብለን ብንገልፀውም ያስኬዳል በሚል ንጽጽር ሐሳቡን ሊያሳዩን ይችላሉ።
★እዚህ ላይ ቅድሚያ ርቀ'ታዊ ሀሳቡ ሳይሆን የሚፈለገው ቀዳሚ አውደ ንባባዊ ትንታኔው ወይም ትርጉሙን ነው መጀመርያ የጸሐፊው(የነቢዩ ወይም የሐዋርያው) ሐሳብ ማግኘትና መረዳት ነው ያለብን። ስለዚህ ምክንያት የተለያዩ ትንታኔዎችን ማየት አለብን።አንዱ ሊቅ ምን ብሎ ተነተነው?ሌላውስ ምን አለ? ማእከላዊ (ሁሉንም ሊቃውንት የሚያቀራርበው) ትንታኔስ የትኛው ነው? በሚሉት ላይ በማተኮር ማጥናት።
እነዚህ ጠቅለልና አጠር ባለ መልኩ በጥናት ሂደት የሚጠቅሙን መመሪያዎች ናቸው።
በቀጣይ ክፍል ኦሪት ዘፍጥረት ትንታኔ እንጀምራለን
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
"19፤ ደግሞ የወንጌልን ምሥጢር በግልጥ እንዳስታውቅ አፌን በመክፈት ቃል ይሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ለምኑ፤"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6:19፤)
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
መዝሙረ ዳዊት 118(119)
"76. ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።
'
'
130. የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።

131. አፌን ከፈትሁ፥ አለከለክሁም፤ ወደ ትእዛዝህ ናፍቄአለሁና።"
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
"5፤ ቆማችሁ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላካችንን እግዚአብሔርን ባርኩ። እንዲህም በሉ። በበረከትና በምስጋና ሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያለው ክቡር ስምህ ይባረክ። "
(መጽሐፈ ነሀምያ 9:5፤)
አሜን!!



tg-me.com/yemetshaf_qdus_tinat/6
Create:
Last Update:

📖የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መግቢያ📖
✞ክፍል አራት✞
🔐አጭር የጥናት መመሪያ🔐

መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ቋንቋ እንደ መጻፉ እግዚአብሔር የጸሐፊዎቹን ቋንቋ፣ ባህል፣ የሚኖሩበት አካባቢ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ፣ስነ ቃል ወዘተ ተጠቅሞ ስላፃፋቸው የመጽሐፉን ክፍል ስናጠና መጀመሪያ ስለፀሐፊው ማንነት ቀጥሎም የስነ ጽሑፉ ቅርፅ ባሕርይ(ዓይነት)፣ የሐገሩ ሰዋስው(አገባብ) ወዘተ መረዳት ያስፈልጋል።ለዛሬ በጥናት ጊዜ የሚጠቅሙን አንኳር ሐሳቦችን እንይ

1ኛ.መመልከት ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
ግምታዊ አሰተሳሰብ ሳንሰጥ እንዲሁም ከሌሎች ወይም በስብከት የሰማነውን ትርጉም ቶሎ ሰጥተን አንለፍ ይልቅ ጥቅሶቹ በደምብ ሐሳባቸውን መረዳት "የተባለውን ነገር እውነት ይገልፃሉ?"ብሎ ማንበብ እንጂ ትርጉም ለመስጠት አለመቸኮል።ጸሐፊው በዚህ ክፍል ምን ማለት እንደፈለገ አንብበን በጥሞና መረዳት። በሚከትሉት ጥያቄዎችም በመደገፍ እውነቱን ማስተዋል ይገባል
★ባለታሪኮቹ እነማን ናቸው? ምን ተሰራ ምንስ ተደረገ? የት ቦታ በምንስ ሁኔታ? መቼ? እንዴት? ለምንስ? ውጤቱስ ምን ነበር? ምንስ ተፈጠረ?
የምናጠናውን ክፍል ከአውደንባቡ ለይተን ማውጣት የለብንም!!

★2ኛ.መተርጎም ፦ምን ማለቱ ነው? የሚለውን በመጠየቅ ፍቺ መስጠት። በአሁኑ ጊዜስ ተመሳሳይ የሆነው ፍቺው ምንድነው? መዝገበ ቃላት በመጠቀም ቃላቶቹን ፣ ሐረጎቹን፣ ቅኔያዊ አነጋገሮችንና ዐረፍተ ነገሮችን መተንተን

★3ኛ.ማዛመድ
ለምን ይህንን ሃሳብ ፣ ሐረግ፣ ቃል ተጠቀመ? ለምንስ ይህንን እዚህ መጥቀስ አስፈለገው? ያሉት የተለያዩ ሃሳቦችስ እንዴት ይዛመዳሉ?
ጠቃሚውን ሃሳብ ማግኘት።
ጎልቶ የሚታየውን መንፈሳዊ ሃሳብ ወይም መልዕክት ለይተን ማውጣት።ከሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች ጋረ መስማማቱን ማረጋገጥ።
ዋናውን መልዕክት ቸል ብለን በጥቃቅን ነገሮች ላይ እንዳናተኩር ያልገባንን ለሌላ ጊዜ ጥናት ማስተላለፍ ወይም ሌሎችን በመጠየቅ መረዳት።

★4ኛ.የተለያዩ ሊቃውንት ትንታኔዎችን መመልከት
የአንዱን ሊቅ ሐሳብ ብቻ በመያዝ ትርጉም ሰጥቶ አይታለፍም!! ምክንያቱም በሊቃውንቱ አፈታት ወይም አተናተን ላይ መራቀቅ ሊኖር ይችላል ማለትም የአውደንባቡ ሐሳብ ሌላ ሊሆን ይችላል ነገር ግን በመራቀቅ እንዲህ ብለን ብንገልፀውም ያስኬዳል በሚል ንጽጽር ሐሳቡን ሊያሳዩን ይችላሉ።
★እዚህ ላይ ቅድሚያ ርቀ'ታዊ ሀሳቡ ሳይሆን የሚፈለገው ቀዳሚ አውደ ንባባዊ ትንታኔው ወይም ትርጉሙን ነው መጀመርያ የጸሐፊው(የነቢዩ ወይም የሐዋርያው) ሐሳብ ማግኘትና መረዳት ነው ያለብን። ስለዚህ ምክንያት የተለያዩ ትንታኔዎችን ማየት አለብን።አንዱ ሊቅ ምን ብሎ ተነተነው?ሌላውስ ምን አለ? ማእከላዊ (ሁሉንም ሊቃውንት የሚያቀራርበው) ትንታኔስ የትኛው ነው? በሚሉት ላይ በማተኮር ማጥናት።
እነዚህ ጠቅለልና አጠር ባለ መልኩ በጥናት ሂደት የሚጠቅሙን መመሪያዎች ናቸው።
በቀጣይ ክፍል ኦሪት ዘፍጥረት ትንታኔ እንጀምራለን
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
"19፤ ደግሞ የወንጌልን ምሥጢር በግልጥ እንዳስታውቅ አፌን በመክፈት ቃል ይሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ለምኑ፤"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6:19፤)
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
መዝሙረ ዳዊት 118(119)
"76. ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።
'
'
130. የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።

131. አፌን ከፈትሁ፥ አለከለክሁም፤ ወደ ትእዛዝህ ናፍቄአለሁና።"
✞❀✞❀✞❀✞❀✞❀✞
"5፤ ቆማችሁ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላካችንን እግዚአብሔርን ባርኩ። እንዲህም በሉ። በበረከትና በምስጋና ሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያለው ክቡር ስምህ ይባረክ። "
(መጽሐፈ ነሀምያ 9:5፤)
አሜን!!

BY የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/yemetshaf_qdus_tinat/6

View MORE
Open in Telegram


የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Why Telegram?

Telegram has no known backdoors and, even though it is come in for criticism for using proprietary encryption methods instead of open-source ones, those have yet to be compromised. While no messaging app can guarantee a 100% impermeable defense against determined attackers, Telegram is vulnerabilities are few and either theoretical or based on spoof files fooling users into actively enabling an attack.

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት from us


Telegram የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
FROM USA