Telegram Group & Telegram Channel
የአፄ ዮሐንስ 1ኛ ዘመነ መንግስት
ከ1659-1674 ዓ.ም


ክፍል አንድ:-

✍🏽.አፄ ዮሐንስ በሚለው መጠሪያ ስም ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ የነገሱት እኒሁ የአፄ ፋሲል ልጅ የሆኑት ናቸው። የአፄ ፋሲል እረፍት ለሕዝብ ሳይወጣ እስከ ልጃቸው ንግስና ድረስ ተደብቆ ነበር። ይኸውም በዙፋን ምክንያት አመፅ እንዳይቀሰቀስ ተሰግቶ የተደረገ ነበር። ያኔ የነገስታቱ ዘር ታጉረው ከሚኖሩበት አምባ ዮሐንስን በማስመጣት እንዲነግሱ አደረጓቸው።
✍🏽.አፄ ዮሐንስ 1ኛ በ1659 ዓ.ም የንግስና ስማቸውን "አእላፍ ሠገድ" አሰኝተው የአባታቸውን መንግስት ይዘው ስራቸውን ማካሄድ ጀመሩ።
✍🏽የመጀመሪያ ስራቸው ያደረጉት የነገስታቱ ልጆች ብቻ በወህኒ አምባ እንደከዚህ ቀደሙ ባሉበት እንዲቆዩ አድርገው፣ለቀሪው መላው እስረኛ ሁሉ ሙሉ ምህረት ማድረግን ነበር።
አፄ ዮሐንስ 1ኛ ለንግስና የተመረጡበት ምክንያት ከልጅነታቸው ጀምረው መንፈሳዊ ት/ት ላይ ያተኮሩና ለደሀ አዛኝ መሆናቸውን በደንብ ይታወቅ ስለነበር ነው።በወህኒ አምባ በለመዱት ስራቸው ሰሌን እየሰሩ ለድሆች በነፃ ይሰጣሉ።እጅግ ደግ ከመሆናቸው የተነሳም"ፃድቁ ዮሃንስ"በሚል መጠሪያቸው ነበር የሚታወቁት፤በዘመናቸው ከፈፀሟቸው ተግባራት ውስጥም የተለያዩ ነገዶችን ለየግላቸው መንደራቸውን ለይተው በየራሳቸው ባህል፣ወግ እና ልማድ እንዲኖሩ ማድረጋቸው ይጠቀሳል።የውጪ ሀገር ዜጎችን በተመለከተም በኢትዮጵያውያን ወግ እና ባህል፣እንዲሁም ሀይማኖት ስር ሆነው መኖር የሚፈልጉትን በነፃነት መኖር እንዲችሉ በመግለፅና በዚህ ካልተስማሙ ግን ወደየመጡበት አገራቸው እንዲመለሱ አውጀዋል፤ይህን መሰሉ አዋጅ ሲታወጅ በኢትዮጵያ ምድር የነበሩ የውጭ ዜጎች በአሪንጎ ሰፍረው ይኖሩ ነበር።ወደ ሀገራቸው ሳይሄዱ በያሉበት የነበሩትም ይገድሉናል ብለው ፈርተው ነበር።ወዲያው "ሊይዙን የመጡ እንደሆነ ሳንዋጋ እጃችንን አንሰጥም ብለዋል" የሚል ወሬ በቤተ መንግስቱ ተሰማ።ስለዚህ ንግግር አዋቂና የዲፕሎማሲ ሰው ግራዝማች ሚካኤል ነው፤ተባለና ተመርጦ ፈረንጆቹ ወዳሉበት ሄዶ"በቆላ ወይም በደጋ በፈለጋችሁት በኩል ወደ አገራችሁ እንድትመለሱ ታዛችኋል"ሲባሉ እነሱም"በቆላ በኩል አድርገን በስናር በኩል ተጉዘን ወደ አገራችን እንገባለን" አሉ።ከዛም ግራ አዝማች ከአሪንጎ ወደ ጎንደር ተመለሱ።
✍🏽ከአፄ ፋሲልና ከእቴጌ እህተክርስቶስ የተወለዱት አፄ ዮሐንስ 1ኛ በዘመናቸው በአባታቸው ጊዜ ይሸፍቱ የነበሩትን የሻንቅላ፣የሀንጋዝ፣የባንጋ፣የዋጅራት ነገዶችን አመፅ አስተናግደዋል።በየክፍሉ እንደራሴያቸውን መልዓከ ክርስቶስን፣የጦር አለቃቸውን ብላቴን ጌታ ገብረልዑልን፣ሹማምንቶቻቸውን እና ደጃዝማች ዘማሪያምን ልከው እያዋጉ፣እራሳቸውም እነ አቤቶ ዮስጦስን፣እነ ፊትአውራሪ ወልደ ብሩክን እያስከተሉ ሄደው ከአገር ወደ አገር እየተዘዋወሩ ሲያዋጉና ሲዋጉ ቆይተው፣የየግዛቱን አመፆች አርግበው በድል አድራጊነት ወደ ጎንደር ለመመለስ ችለዋል።ከጦር ሜዳ መልስም "ከሕዝብ ከፍተኛ ቀረጥና ግብር አልወስድም"በማለት ራሳቸው በሚሰሩት ሰሌን ይተዳደሩ ጀመር።የተረፈውንም ለድሆች በመመፅወት ይኖሩ ነበር እንጂ የተንደላቀቀ ህይወትን ንቀውት ነበር ጊዜያቸውን ያሳለፉት።ሆኖም ሰፊ የሰላም ጊዜ እንዳይኖራቸው የሀገር ውስጥ አመፅ መበራከት አገዳቸው።በ1667 ዓ.ም በአገው ምድር ያመፁትን ተዋግተው ያስገብሯቸው ዘንድ ጉዞ ጀመሩ።
✍🏽በዚያ ወቅት ደግሞ በአገዎች ዘንድ ብዙ ተላላፊ በሽታዎች በርክተው ህዝቡ ማለቅ ጀምሮ ነበር።ንጉሡ እንደደረሱም ሠባቱ የአገው ምድር ነዋሪዎች የሸፈቱት ሁሉ ለንጉሠ ነገስቱ ሰገዱላቸው።ሳጥናቸውንም እየከፈቱ ወርቅ ብርና የዝሆን ጥርስ እጅ መንሺያና ይቅርታ መጠየቂያ ሠጡዋቸው።ውጊያውም ቀርቶ ሁኔታው በሠላም ተፈታ።
.
.
.
ይቀጥላል



tg-me.com/yekidst_hager777/2489
Create:
Last Update:

የአፄ ዮሐንስ 1ኛ ዘመነ መንግስት
ከ1659-1674 ዓ.ም


ክፍል አንድ:-

✍🏽.አፄ ዮሐንስ በሚለው መጠሪያ ስም ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ የነገሱት እኒሁ የአፄ ፋሲል ልጅ የሆኑት ናቸው። የአፄ ፋሲል እረፍት ለሕዝብ ሳይወጣ እስከ ልጃቸው ንግስና ድረስ ተደብቆ ነበር። ይኸውም በዙፋን ምክንያት አመፅ እንዳይቀሰቀስ ተሰግቶ የተደረገ ነበር። ያኔ የነገስታቱ ዘር ታጉረው ከሚኖሩበት አምባ ዮሐንስን በማስመጣት እንዲነግሱ አደረጓቸው።
✍🏽.አፄ ዮሐንስ 1ኛ በ1659 ዓ.ም የንግስና ስማቸውን "አእላፍ ሠገድ" አሰኝተው የአባታቸውን መንግስት ይዘው ስራቸውን ማካሄድ ጀመሩ።
✍🏽የመጀመሪያ ስራቸው ያደረጉት የነገስታቱ ልጆች ብቻ በወህኒ አምባ እንደከዚህ ቀደሙ ባሉበት እንዲቆዩ አድርገው፣ለቀሪው መላው እስረኛ ሁሉ ሙሉ ምህረት ማድረግን ነበር።
አፄ ዮሐንስ 1ኛ ለንግስና የተመረጡበት ምክንያት ከልጅነታቸው ጀምረው መንፈሳዊ ት/ት ላይ ያተኮሩና ለደሀ አዛኝ መሆናቸውን በደንብ ይታወቅ ስለነበር ነው።በወህኒ አምባ በለመዱት ስራቸው ሰሌን እየሰሩ ለድሆች በነፃ ይሰጣሉ።እጅግ ደግ ከመሆናቸው የተነሳም"ፃድቁ ዮሃንስ"በሚል መጠሪያቸው ነበር የሚታወቁት፤በዘመናቸው ከፈፀሟቸው ተግባራት ውስጥም የተለያዩ ነገዶችን ለየግላቸው መንደራቸውን ለይተው በየራሳቸው ባህል፣ወግ እና ልማድ እንዲኖሩ ማድረጋቸው ይጠቀሳል።የውጪ ሀገር ዜጎችን በተመለከተም በኢትዮጵያውያን ወግ እና ባህል፣እንዲሁም ሀይማኖት ስር ሆነው መኖር የሚፈልጉትን በነፃነት መኖር እንዲችሉ በመግለፅና በዚህ ካልተስማሙ ግን ወደየመጡበት አገራቸው እንዲመለሱ አውጀዋል፤ይህን መሰሉ አዋጅ ሲታወጅ በኢትዮጵያ ምድር የነበሩ የውጭ ዜጎች በአሪንጎ ሰፍረው ይኖሩ ነበር።ወደ ሀገራቸው ሳይሄዱ በያሉበት የነበሩትም ይገድሉናል ብለው ፈርተው ነበር።ወዲያው "ሊይዙን የመጡ እንደሆነ ሳንዋጋ እጃችንን አንሰጥም ብለዋል" የሚል ወሬ በቤተ መንግስቱ ተሰማ።ስለዚህ ንግግር አዋቂና የዲፕሎማሲ ሰው ግራዝማች ሚካኤል ነው፤ተባለና ተመርጦ ፈረንጆቹ ወዳሉበት ሄዶ"በቆላ ወይም በደጋ በፈለጋችሁት በኩል ወደ አገራችሁ እንድትመለሱ ታዛችኋል"ሲባሉ እነሱም"በቆላ በኩል አድርገን በስናር በኩል ተጉዘን ወደ አገራችን እንገባለን" አሉ።ከዛም ግራ አዝማች ከአሪንጎ ወደ ጎንደር ተመለሱ።
✍🏽ከአፄ ፋሲልና ከእቴጌ እህተክርስቶስ የተወለዱት አፄ ዮሐንስ 1ኛ በዘመናቸው በአባታቸው ጊዜ ይሸፍቱ የነበሩትን የሻንቅላ፣የሀንጋዝ፣የባንጋ፣የዋጅራት ነገዶችን አመፅ አስተናግደዋል።በየክፍሉ እንደራሴያቸውን መልዓከ ክርስቶስን፣የጦር አለቃቸውን ብላቴን ጌታ ገብረልዑልን፣ሹማምንቶቻቸውን እና ደጃዝማች ዘማሪያምን ልከው እያዋጉ፣እራሳቸውም እነ አቤቶ ዮስጦስን፣እነ ፊትአውራሪ ወልደ ብሩክን እያስከተሉ ሄደው ከአገር ወደ አገር እየተዘዋወሩ ሲያዋጉና ሲዋጉ ቆይተው፣የየግዛቱን አመፆች አርግበው በድል አድራጊነት ወደ ጎንደር ለመመለስ ችለዋል።ከጦር ሜዳ መልስም "ከሕዝብ ከፍተኛ ቀረጥና ግብር አልወስድም"በማለት ራሳቸው በሚሰሩት ሰሌን ይተዳደሩ ጀመር።የተረፈውንም ለድሆች በመመፅወት ይኖሩ ነበር እንጂ የተንደላቀቀ ህይወትን ንቀውት ነበር ጊዜያቸውን ያሳለፉት።ሆኖም ሰፊ የሰላም ጊዜ እንዳይኖራቸው የሀገር ውስጥ አመፅ መበራከት አገዳቸው።በ1667 ዓ.ም በአገው ምድር ያመፁትን ተዋግተው ያስገብሯቸው ዘንድ ጉዞ ጀመሩ።
✍🏽በዚያ ወቅት ደግሞ በአገዎች ዘንድ ብዙ ተላላፊ በሽታዎች በርክተው ህዝቡ ማለቅ ጀምሮ ነበር።ንጉሡ እንደደረሱም ሠባቱ የአገው ምድር ነዋሪዎች የሸፈቱት ሁሉ ለንጉሠ ነገስቱ ሰገዱላቸው።ሳጥናቸውንም እየከፈቱ ወርቅ ብርና የዝሆን ጥርስ እጅ መንሺያና ይቅርታ መጠየቂያ ሠጡዋቸው።ውጊያውም ቀርቶ ሁኔታው በሠላም ተፈታ።
.
.
.
ይቀጥላል

BY ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/yekidst_hager777/2489

View MORE
Open in Telegram


ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Start with a fresh view of investing strategy. The combination of risks and fads this quarter looks to be topping. That means the future is ready to move in.Likely, there will not be a wholesale shift. Company actions will aim to benefit from economic growth, inflationary pressures and a return of market-determined interest rates. In turn, all of that should drive the stock market and investment returns higher.

Dump Scam in Leaked Telegram Chat

A leaked Telegram discussion by 50 so-called crypto influencers has exposed the extraordinary steps they take in order to profit on the back off unsuspecting defi investors. According to a leaked screenshot of the chat, an elaborate plan to defraud defi investors using the worthless “$Few” tokens had been hatched. $Few tokens would be airdropped to some of the influencers who in turn promoted these to unsuspecting followers on Twitter.

ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ from us


Telegram ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ
FROM USA