" በአስር ቀናት ዉስጥ የ19 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/94660
Create:
Last Update:
Last Update:
" በአስር ቀናት ዉስጥ የ19 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA


Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94660