Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94529-94530-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94529 -
Telegram Group & Telegram Channel
“ ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም።  ” - ኢሕአፓ ስለታሰረው አመራሩ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የአዲስ አበባ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ አባሉ አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንደታሰሩበት ገልጿል።

ፓርቲው አመራሬ “በሐሰተኛ ፍረጃ ነው” የታሰሩብኝ ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት መጋቢብሉይ አብርሃም ሃይማኖት በሰጡት ቃል ፥ "  የካቲት 6/2017 ዓ/ም ከቤታቸው በፓሊስ ተወስደው ነው የታሰሩት።  ' ፋኖ ይደግፋል '  በሚል ሐሰተኛ ውንጀላ ነው የተወነጀለው " ሲሉ
ገልጸዋል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት በዝርዝር ምን አሉ ? 

“ ሰላማዊ ታጋዮችን በሐሰተኛ መረጃ እያሸማቀቁ እያሰሩ፤ ጋዜጠኞችን እያሳደዱ ሀገር ሰላም ማድረግ አይቻልም። ስለዚህ ሰላም ጠሉ ራሱ መንግስት እንደሆነ ነው እያረጋገጠልን ያለው።

አቶ ይሳቅ ከተባለበት ጉዳይ ጋር የሚያያይዘው አንዳችም ነገር የለም። መንግስት ሕግ ማክበር እንዳለበት የዘነጋው ይመስለኛል። መንግስት ሕገ መንግስቱን አክብሮ ነው የሚያስከብረው፤ ራሱ እየደፈጠጠ መሆን የለበትም።

ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ግን ‘የአፍሪካ ህብረትን ለመበጥበጥ፣ መሪዎችን ለመግደል’ የሚል ሐሰተኛ ፈጠራ ሲያቀናብሩ አእምሯቸው እንዴት አቀናበረው ? ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል።

ከዚህ በፊት ዓርዓያ ተስፋማርያም በሚባል ጋዜጠኛ ነኝ በሚል ግለሰብ ይሄው አባላችን ታስሮ በጩኸት ወጥቷል። አሁንም በሐሰተኛ ቅንብር፣ ከመንግስት አካላት ጋር ያላቸው ግንኙነትን በመጠቀም ታስሯል ” ብለዋል።

አመራሩ ከ“ፋኖ” ጋር በተገናኘ የተጠረጠሩት ፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን ከምን ጋር አገናኝቶት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ በኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ካሳ እንዳልተከፈላቸው በማጋለጣቸው ነው ሲሉ ጠቅሰዋል። 

አክለው፣ “ ያንን ተከትሎ ኢሕአፓን ለማሸማቀቅና ቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጠንካራ ሰላማዊ ትግል እንዳያደርግ ሆን ተብሎ ለማስፈራራት የተቀናበረ ቅንብር ነው ” ብለው፣ ፓርቲው በዚህ እንደማይሸማቀቅ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የፌደራል ፓሊስ የምርመራ ጊዜ ማጣሪያ የጠየቀበት ደብዳቤ፣ ከአቶ ይሳቅ ጋር 13 ግለሰቦችን ጠቅሶ " በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው " ቡድን ግንኙነት አላቸው በሚል ይወነጅላል።

ፓሊስ፣ “ ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት ” የ14 ቀናት የቀጠሮ ጊዜ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረቡን ደብዳቤው ያትታል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ከንቲባ በበኩላቸው፣ “ ሰኞ ፍርድ ቤት ለኛ ቀጠሮ ሰጥቶናል የፌደራል ፓሊስ የ14 ቀን ቀጠሮን ውድቅ በማድረግ ‘ተጨባጭ መረጃ ካላችሁ አምጡ’ በማለት” ብለዋል። 

“ ፍርድ ቤቱም ‘እንደዚህ አይነት ሐሰተኛ ቅንብሮች እየተለመደ ስለመጡ ተጨባጭ ነገር ካለ አምጡ አለዚያ ጊዜ ቀጠሮ አልሰጣችሁም’ ብሎ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል ” ነው ያሉት።

13ቱም “ተጠርጣሪዎች” የፓርቲው አካላት ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው ተቀዳሚ ፕሬዛዳንቱ፤ ከአቶ ይሳቅ ውጪ ያሉት 12 ተጠረጠሩ ተብለው የታሰሩ ግለሰቦች ከፓርቲው ጋ ግንኙነት እንደሌላቸው አስረድተዋል።

“ ነጋዴዎች አሉ ምንም ፓለቲካ ውስጥ የሌሉ። በተጨባጭ መረጃ ያለን አንድ ካድሬ ከጠላ ይፈርጅህና ለወራት ታሽተህ ትለቀቃለህ። ዜጎችን ማሸማቀቂያ፣ ማሰቃያ ሆኗል የፍትህ ስርዓቱ ” ሲሉ ወቅሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/94529
Create:
Last Update:

“ ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም።  ” - ኢሕአፓ ስለታሰረው አመራሩ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የአዲስ አበባ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ አባሉ አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንደታሰሩበት ገልጿል።

ፓርቲው አመራሬ “በሐሰተኛ ፍረጃ ነው” የታሰሩብኝ ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት መጋቢብሉይ አብርሃም ሃይማኖት በሰጡት ቃል ፥ "  የካቲት 6/2017 ዓ/ም ከቤታቸው በፓሊስ ተወስደው ነው የታሰሩት።  ' ፋኖ ይደግፋል '  በሚል ሐሰተኛ ውንጀላ ነው የተወነጀለው " ሲሉ
ገልጸዋል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት በዝርዝር ምን አሉ ? 

“ ሰላማዊ ታጋዮችን በሐሰተኛ መረጃ እያሸማቀቁ እያሰሩ፤ ጋዜጠኞችን እያሳደዱ ሀገር ሰላም ማድረግ አይቻልም። ስለዚህ ሰላም ጠሉ ራሱ መንግስት እንደሆነ ነው እያረጋገጠልን ያለው።

አቶ ይሳቅ ከተባለበት ጉዳይ ጋር የሚያያይዘው አንዳችም ነገር የለም። መንግስት ሕግ ማክበር እንዳለበት የዘነጋው ይመስለኛል። መንግስት ሕገ መንግስቱን አክብሮ ነው የሚያስከብረው፤ ራሱ እየደፈጠጠ መሆን የለበትም።

ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ግን ‘የአፍሪካ ህብረትን ለመበጥበጥ፣ መሪዎችን ለመግደል’ የሚል ሐሰተኛ ፈጠራ ሲያቀናብሩ አእምሯቸው እንዴት አቀናበረው ? ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል።

ከዚህ በፊት ዓርዓያ ተስፋማርያም በሚባል ጋዜጠኛ ነኝ በሚል ግለሰብ ይሄው አባላችን ታስሮ በጩኸት ወጥቷል። አሁንም በሐሰተኛ ቅንብር፣ ከመንግስት አካላት ጋር ያላቸው ግንኙነትን በመጠቀም ታስሯል ” ብለዋል።

አመራሩ ከ“ፋኖ” ጋር በተገናኘ የተጠረጠሩት ፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን ከምን ጋር አገናኝቶት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ በኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ካሳ እንዳልተከፈላቸው በማጋለጣቸው ነው ሲሉ ጠቅሰዋል። 

አክለው፣ “ ያንን ተከትሎ ኢሕአፓን ለማሸማቀቅና ቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጠንካራ ሰላማዊ ትግል እንዳያደርግ ሆን ተብሎ ለማስፈራራት የተቀናበረ ቅንብር ነው ” ብለው፣ ፓርቲው በዚህ እንደማይሸማቀቅ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የፌደራል ፓሊስ የምርመራ ጊዜ ማጣሪያ የጠየቀበት ደብዳቤ፣ ከአቶ ይሳቅ ጋር 13 ግለሰቦችን ጠቅሶ " በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው " ቡድን ግንኙነት አላቸው በሚል ይወነጅላል።

ፓሊስ፣ “ ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት ” የ14 ቀናት የቀጠሮ ጊዜ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረቡን ደብዳቤው ያትታል።

የፓርቲው ተቀዳሚ ከንቲባ በበኩላቸው፣ “ ሰኞ ፍርድ ቤት ለኛ ቀጠሮ ሰጥቶናል የፌደራል ፓሊስ የ14 ቀን ቀጠሮን ውድቅ በማድረግ ‘ተጨባጭ መረጃ ካላችሁ አምጡ’ በማለት” ብለዋል። 

“ ፍርድ ቤቱም ‘እንደዚህ አይነት ሐሰተኛ ቅንብሮች እየተለመደ ስለመጡ ተጨባጭ ነገር ካለ አምጡ አለዚያ ጊዜ ቀጠሮ አልሰጣችሁም’ ብሎ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል ” ነው ያሉት።

13ቱም “ተጠርጣሪዎች” የፓርቲው አካላት ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው ተቀዳሚ ፕሬዛዳንቱ፤ ከአቶ ይሳቅ ውጪ ያሉት 12 ተጠረጠሩ ተብለው የታሰሩ ግለሰቦች ከፓርቲው ጋ ግንኙነት እንደሌላቸው አስረድተዋል።

“ ነጋዴዎች አሉ ምንም ፓለቲካ ውስጥ የሌሉ። በተጨባጭ መረጃ ያለን አንድ ካድሬ ከጠላ ይፈርጅህና ለወራት ታሽተህ ትለቀቃለህ። ዜጎችን ማሸማቀቂያ፣ ማሰቃያ ሆኗል የፍትህ ስርዓቱ ” ሲሉ ወቅሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94529

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Start with a fresh view of investing strategy. The combination of risks and fads this quarter looks to be topping. That means the future is ready to move in.Likely, there will not be a wholesale shift. Company actions will aim to benefit from economic growth, inflationary pressures and a return of market-determined interest rates. In turn, all of that should drive the stock market and investment returns higher.

Export WhatsApp stickers to Telegram on iPhone

You can’t. What you can do, though, is use WhatsApp’s and Telegram’s web platforms to transfer stickers. It’s easy, but might take a while.Open WhatsApp in your browser, find a sticker you like in a chat, and right-click on it to save it as an image. The file won’t be a picture, though—it’s a webpage and will have a .webp extension. Don’t be scared, this is the way. Repeat this step to save as many stickers as you want.Then, open Telegram in your browser and go into your Saved messages chat. Just as you’d share a file with a friend, click the Share file button on the bottom left of the chat window (it looks like a dog-eared paper), and select the .webp files you downloaded. Click Open and you’ll see your stickers in your Saved messages chat. This is now your sticker depository. To use them, forward them as you would a message from one chat to the other: by clicking or long-pressing on the sticker, and then choosing Forward.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA