Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94453-94454-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94454 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን  ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ተው ብለው እምቢ ብሎኛል"  - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።

ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም  እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል። 

" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።  

" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።    

" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።

ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።

ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ  ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።

ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            



tg-me.com/tikvahethiopia/94454
Create:
Last Update:

" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን  ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ተው ብለው እምቢ ብሎኛል"  - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።

ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም  እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል። 

" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።  

" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።    

" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።

ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።

ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ  ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።

ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94454

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

The global forecast for the Asian markets is murky following recent volatility, with crude oil prices providing support in what has been an otherwise tough month. The European markets were down and the U.S. bourses were mixed and flat and the Asian markets figure to split the difference.The TSE finished modestly lower on Friday following losses from the financial shares and property stocks.For the day, the index sank 15.09 points or 0.49 percent to finish at 3,061.35 after trading between 3,057.84 and 3,089.78. Volume was 1.39 billion shares worth 1.30 billion Singapore dollars. There were 285 decliners and 184 gainers.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA