" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ተው ብለው እምቢ ብሎኛል" - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ
በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።
ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል።
" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።
" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።
" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።
ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።
የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።
ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።
ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።
ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል።
" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።
" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።
" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።
ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።
የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።
ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።
ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/94453
Create:
Last Update:
Last Update:
" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ተው ብለው እምቢ ብሎኛል" - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ
በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።
ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል።
" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።
" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።
" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።
ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።
የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።
ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።
ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።
ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል።
" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።
" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።
" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።
ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።
የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።
ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።
ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA


Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94453