Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94453-94454-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94453 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን  ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ተው ብለው እምቢ ብሎኛል"  - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።

ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም  እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል። 

" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።  

" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።    

" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።

ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።

ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ  ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።

ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            



tg-me.com/tikvahethiopia/94453
Create:
Last Update:

" ጊዚያዊ መንግስት ይሁን ጊዚያዊ አስተዳደር ተቀባይነት የለውም ! ... ፃድቃን  ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ተው ብለው እምቢ ብሎኛል"  - የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮጵያ ፓለቲካ በአነጋጋሪነታቸው የሚታወቁት ከቀንደኞቹ የህወሓት ነባር ታጋዮች አንዱ የሆኑት ከ80 ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩት ስብሓት ነጋ የካቲት 11/2017 ዓ.ም የህወሓት 50 ዓመት የትግል ምስረታ ምክንያት በማድረግ የደርጅቱ ልሳን ለሆነው ወይን ጋዜጣ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ 90 ደቂቃ ያህል ርዝማኔ ያለው የህወሓት ነባር ታጋይ ስብሓት ነጋ በትግርኛ የሰጡት ቃለ-መጠይቅ ተከታትሎታል።

ህወሓት ከተመሰረተ ጀምሮ ውስጣዊ የአመራር መከፋፈል ፈተና እንዳልተለየው የገለፁት አቦይ ስብሓት ነጋ ፥ " በ1969 ዓ.ም  እንደ አንድ የፓለቲካ ድርጅት በተመሰረተ ማግስት ያጋጠመው የአመራር መከፋፈል በመጋዳደል ሳይሆን በፓለቲካዊ ክርክር ነው የፈታው " ብለዋል። 

" ህወሓት ከመመስረትዋ በፊት ሁሉም ይንቁን ነበር " በማለት ይንቁዋቸው የነበሩት በስም ያልጠቀሱት ስብሓት " እንደ ሰው የሚቆጥረን አልነበረም ፤ ' ትግራይ ከበላ ከጠጣ ፓለቲካዊ ስልጣን ምን ይፈይድለታል ? ' የሚለውን ስላቅ የቀየረው ህወሓት ነው " ብለዋል።  

" ህወሓት ሁሌ ተማሪ ህዝባዊ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በመሆኑ ይታወቃል ያሉት የቀድሞ ታጋይ " ባለፉት 50 ዓመታት በህወሓት ላይ ያልተሞከረ ክፋት አልነበረም፤ ድርጅቱ ግን ህዝብ መሰረት ያደረገ ትግል በማካሄድ ችግሮቹ ተሻግሮዋቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ1969 ዓ.ም እስከ 1971 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ኢድዩ (የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት ) የተባለ ፓርቲ ህወሓትን ከገፀ ምድር ለማጣፋት ያለመ ያልተሳካ ዘመቻ ማወጁ ፣ 1977 ዓ.ም ከባድ የአመራር መከፋፈል አጋጥሟት እንደነበረ ያወሱት ስብሓት " ፈተናዎቹ በፅናት እና በዴሞክራሲያዊ ክርክር መታለፍ ችለዋል " ሲሉ አብራርተዋል።    

" ቀደም ሲልም አሁንም ከህወሓት ያፈነገጡት አመራሮች ከጠላት በላይ ጠላት ናቸው " ሲሉ የፈረጁት ስብሃት " ፃድቃን ከ93 ዓ.ም ጀምሮ  የCIA አባል በመሆን ህወሓት ለማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል  ፤ ተው ብለው እምቢ ብሎኛል " ሲሉ ከሰዋል። 

ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደ ከሃዲ ፣ ቂመኛ የህወሓት እና የትግራይ መንግስት መዋቅር አፍራሽ መሆኑን በመግለፅ እንደማይቀበሉት እና በፅኑ እንደሚቃወሙት አሳውቀዋል።

ስብሃት " የፌደራሊዝም የፓለቲካዊ አስተዳደር ስርዓት በማሞካሸት ፤ ህወሓት የፌደራል ስርዓት ለማጠናከር ከመሰል የፓለቲካ ፓርቲዎች በማበር እንዲታገል እና ችግሮቹ እንዲፈታ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት ሳይሸራረፍ እንዲተገበር እና እንዲከበር ህወሓት መታገለ እንዳለበተ የተናገሩት ስብሓት " መሪዎች ከህዝብ መነጠል የለባቸውም ፤ ህዝባቸው እንዳይከፋፈል መታገል መምራት አለባቸው የህወሓት ድምፅ ይሰማ " ሲሉ ለወይን ጋዜጣ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም በተካሄደው የትግራይ ጦርነት በፌደራል መንግስት ተማርከው በእስር ከቆዩ በኋላ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በምህረት የተለቀቁት የቀድሞ የህወሓት ታጋይ እና ከፍተኛ አመራር ስብሓት ነጋ አሁን ለህክምና በአሜሪካ ይገኛሉ።

ስብሓት ነጋ ከ ቀድሞው የደርግ ስርዓት መውደቅ በኋላ የኢፈርት ኢንደውመንት የባለ አደራ ቦርድ  ሰብሳቢ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰላም እና ምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርነት ጨምሮ በበርካታ የስልጣን እርከኖች የቦርድ አባል በመሆን ሰርተዋል።

ህወሓትን በሊቀ-መንበርነት የመሩት ስብሓት ነጋ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ለቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በራሳቸው ፍቃድ የሊቀመንበር ስልጣናቸው አሳልፈው መስጠታቸው በፓርቲያቸው ይነግርላቸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94453

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram auto-delete message, expiring invites, and more

elegram is updating its messaging app with options for auto-deleting messages, expiring invite links, and new unlimited groups, the company shared in a blog post. Much like Signal, Telegram received a burst of new users in the confusion over WhatsApp’s privacy policy and now the company is adopting features that were already part of its competitors’ apps, features which offer more security and privacy. Auto-deleting messages were already possible in Telegram’s encrypted Secret Chats, but this new update for iOS and Android adds the option to make messages disappear in any kind of chat. Auto-delete can be enabled inside of chats, and set to delete either 24 hours or seven days after messages are sent. Auto-delete won’t remove every message though; if a message was sent before the feature was turned on, it’ll stick around. Telegram’s competitors have had similar features: WhatsApp introduced a feature in 2020 and Signal has had disappearing messages since at least 2016.

The lead from Wall Street offers little clarity as the major averages opened lower on Friday and then bounced back and forth across the unchanged line, finally finishing mixed and little changed.The Dow added 33.18 points or 0.10 percent to finish at 34,798.00, while the NASDAQ eased 4.54 points or 0.03 percent to close at 15,047.70 and the S&P 500 rose 6.50 points or 0.15 percent to end at 4,455.48. For the week, the Dow rose 0.6 percent, the NASDAQ added 0.1 percent and the S&P gained 0.5 percent.The lackluster performance on Wall Street came on uncertainty about the outlook for the markets following recent volatility.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA