" ከጦርነቱ በፊት ነጋዴዎች ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር አድጓል " - ከትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/94439
Create:
Last Update:
Last Update:
" ከጦርነቱ በፊት ነጋዴዎች ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር አድጓል " - ከትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ተበድረውት የነበረው 32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ማደጉን የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አሳውቋል።
ም/ቤቱ ይህን ያሳወቀው ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።
የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዘዳንት አቶ በሪሁን ሃፍቱ ምን አሉ ?
➡️ ነጋዴዎች ከጦርነቱ በፊት ከባንክ ወስደውት ነበረው የባንክ እዳ በ5 አመት ወስጥ ከ32 ቢሊዮን ብር አሁን ከነወለዱ ወደ 80 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
➡️ ተከስቶ የነበረው ጦርነት ብዙ ሀብት አውድሟል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን አጥፍቷል፣ ቀሪዎችንም ከንግድ እንቅስቃሴ ውጭ አድርጎ የገበያ ትስስራቸውን እንዲያጡ አድርጓል።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የጠፉት የባንክ ብድር ይዘው ነው።
➡️ የባንክ እዳ ይዘው የወደሙ የንግድ ተቋማትን ወደ መደበኛ ሥርዓት ለመመለስ ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ባለሀብቱ ፈልጎ ባላመጣው ጦርነት ተዳክሟል።
➡️ በክልሉ ያሉ ባለሀብቶች ንብረታቸው መውደሙ እና ሀብታቸው መጥፋቱ ሳያንስ እዳቸውን ከነወለዱ እና ከነቅጣቱ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ነው። ይህም አግባባብ አደለም። ምክኒያቱም ባለሃብቶች ጦርነቱን ፈልገውት አይደለም ያመጡት።
➡️ የወደሙ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ተመልስው ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ ሳይፈጠር ባለሃብቶች ባልሰሩበት የተበደሩትን እዳ ከነወለዱ እንዲከፍሉ መደረጉ ተገቢ አይደለም። መከፈል ግዴታም ከሆነም ደግሞ ቢያንስ እየሰሩ እንዲከፍሉ ልዩ ማበረታቻ ያሰፈልጋቸዋል።
➡️ የወደሙትን በአዲስ ለመተካት የተዳከሙትን ደግሞ ለማነቃቃት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ያን ማድረግ የሚቻል ከሆነ ነጋዴው ነግዶ አትርፎ አዲስ ግብር ከፋይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረበትን እዳም የመክፈል አቅም ይኖረዋል።
➡️ አሁን ያለብን ትልቁ ችግር ተጨማሪ ድጋፍ አለማግኘት ነው። ባንኮች ተጨማሪ ብድር ለመስጠትም እየተቸገሩ ነው።
➡️ ባለሃብቶች ከጦርነቱ በፊት የተበደሩት እዳ ወለዱም ከዛሬ ነገ እየጨመረ ነው ያለው ፤ አይደለም ሰርቶ ማትረፍ ይቅርና ስራ በቆመበት እና ንብረት በወደመበት ወቅትም ወለዱ እየታሰበ ነው ያ ወለድ ደግሞ የወለድ ወለድ ቅጣት እየታሰበበት ነው።
➡️ ያለው ችግር የተለየ የብደር ጥቅል ካልተዘየደለት አሁን ባለው አሰራር የሚፈታ አይደለም።
➡️ የወደመው ንብረት በቢሊዮን የሚገመት ነው በዚህ ላይ ደግሞ የኢኮኖሚው ማሻሽያ ሲጨመር ችግሩን የከፋ አድርጎታል።
➡️ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ ባለፉት ሁለት አመታት ለክልሉ ባለሃብቶች የቀረበው ብድር 2 ቢሊዮን ብር የማይሞላ ነው ይህም ከችግሩ ስፋት ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም።
➡️ በቅረቡ ከብሄራዊ ባንክ ጋር ውይይት ተደርጎ ነበር በዚህም ነጋዴዎች በሐራጅ ለመሸጥ ጊዜውን ለአንድ አመት እንዲራዝም ተደርጓል ግን ይህ በቂ አይደለም።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA


Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94439