Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94341-94342-94343-94344-94345-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94344 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን ! ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " - በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የወለዱት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ

የመቐለ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የመታቀፋቸው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል።

የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በእናቲቱ መኖሪያ የተዘጋጀውን የክርስትና ድግስ ላይ ተገኝቶ ያጠናቀረውን ፕሮግራም ከትላንት ጀምሮ በሰፊው ህዝብ ጋር ሲዳረስ ነበር።

እናቲቱ በ76 ዓመታቸው መውለዳቸው በዓለም የድንቃድንቅ መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ያለመ የ ' X ' ዘመቻም አለ።

የማህበራዊ ትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች " እናቲቱ በተለመደው ተፈጥሯዊ መንገድ ነው የውለዱት " ፤ " የለም በህክምና ቴክኖሎጂ በመታገዝ ነው ልጃቸውን የታቀፉት " የሚሉ ክርክሮች በማንሳት ሲፅፉ ታይተዋል።

እናቲቱ በድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን እና ሰግለለት ለተባለ ዩቱብ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የተከራካሪዎቹን ጥያቄ ያልመለሰ ድፍን ያለ እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

የመቐለው አባላችን ፤ እናቲቱ በትግርኛ ቋንቋ ለሚድያዎች የሰጡት ቃለ-መጠይቅ እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ያገኘውን መረጃ ከታማኝ የመረጃ ምንጭ ጋር ለማቀናጀት ጥረት አድርጓል።

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ ከዚህ በፊት ልጅ  እንዳልወለዱ ፤ የአሁኑ የመጀመሪያ ልጃቸው መሆኑን በልጃቸው ክርስትና ቀን በአንደበታቸው አረጋግጠዋል። 

ወ/ሮ መድህን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ፅንሳቸውን እስከ 8 ወር ድረስ ደብቀውት እንደነበር ከመግለፅ ባለፈ በተለመደው መንገድ ነው የወለዱት ወይስ በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ (IVF or In Vitro Fertilization) ጥበብ ያሉት ነገር የለም።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከታማኝ ምንጭ ባገኘው መረጃ እናቲቱ የወለዱት በኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለትም የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ መሆኑን ተረድቷል።

ወ/ሮ መድሂን ህክምናውን ለማግኘት ወደ ህንድ ተጉዘዋል።

በዚያው ፅንሱ የ3 ወር ዕድሜ እስኪ ሞላው ድረስ ቆይተዋል።

ከሦስተኛው እስከ ወሊድ ባሉት ጊዜያት የፅንስ ክትትል በመቐለ በሚገኝ አንድ የግል ህክምና ተከታትለው በቀዶ ህክምና ለመውለድ መቻላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

በኢትዮጵያ የወሊድ ህክምና በህግ የተፈቀደው IVF / In Vitro Fertilization የህክምና ጥበብ በመቐለ ጨምሮ በአዲስ አበባ እንደሚሰጥ እየታወቀ እናቲቱ ለምን ውጭ ድረስ ለመጓዝ እንደፈለጉ የታወቀ ነገር የለም።

በ76 ዓመታቸው ልጅ ለማቀፍ የቻሉት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ እሳቸውም ልጃቸውም በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።


" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት ፤ በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን። ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ. በመስረከም 7/2019 የህንድዋ አንድህራ ፕራደሽ ግዛት ተወላጅ የሆኑት ወ/ሮ ማንጋያማ ያራማቲ በ73 ዓመታቸው በIVF ልጅ በማግኘት በእድሜ ትልቋ ተብለው ነበር።

ባለፈው ዓመት ሳፊና ናሙኩዋያ የተባሉ ኡጋንዳዊ ሴት በIVF ህክምና የመንትያ ልጆች እናት መሆን እንደቻሉ በስፋት ተዘግቦ ነበር።

እንደ አንድ የጤና መረጃ አሜሪካ ውስጥ ከሚወለዱት ህጻናት 2% የሚሆኑት በIVF, or  In Vitro Fertilization የህክምና መንገድ ሲሆን ከ8 ሚሊዮን በላይ ህፃናት በዚህ መንገድ ተወልደዋል።

NB. ኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለት የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ ነው። በላብራቶሪ ውስጥ የተፈጠረው ፅንስ በሚፈለገው ደረጃ እድገቱን ከቀጠለ በኋላ ወደ ሴቷዋ ማህፀን በማስገባት የተፈጥሮ እርግዝና ሂደቱን እንዲቀጥል የሚደረግ ይሆናል፡፡

በዚህ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ የጤና ባለሙያ ማብራሪያ ለማቅረብ ጥረት ያደርጋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/94344
Create:
Last Update:

" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን ! ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " - በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የወለዱት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ

የመቐለ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የመታቀፋቸው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል።

የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በእናቲቱ መኖሪያ የተዘጋጀውን የክርስትና ድግስ ላይ ተገኝቶ ያጠናቀረውን ፕሮግራም ከትላንት ጀምሮ በሰፊው ህዝብ ጋር ሲዳረስ ነበር።

እናቲቱ በ76 ዓመታቸው መውለዳቸው በዓለም የድንቃድንቅ መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ያለመ የ ' X ' ዘመቻም አለ።

የማህበራዊ ትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች " እናቲቱ በተለመደው ተፈጥሯዊ መንገድ ነው የውለዱት " ፤ " የለም በህክምና ቴክኖሎጂ በመታገዝ ነው ልጃቸውን የታቀፉት " የሚሉ ክርክሮች በማንሳት ሲፅፉ ታይተዋል።

እናቲቱ በድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን እና ሰግለለት ለተባለ ዩቱብ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የተከራካሪዎቹን ጥያቄ ያልመለሰ ድፍን ያለ እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

የመቐለው አባላችን ፤ እናቲቱ በትግርኛ ቋንቋ ለሚድያዎች የሰጡት ቃለ-መጠይቅ እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ያገኘውን መረጃ ከታማኝ የመረጃ ምንጭ ጋር ለማቀናጀት ጥረት አድርጓል።

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ ከዚህ በፊት ልጅ  እንዳልወለዱ ፤ የአሁኑ የመጀመሪያ ልጃቸው መሆኑን በልጃቸው ክርስትና ቀን በአንደበታቸው አረጋግጠዋል። 

ወ/ሮ መድህን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ፅንሳቸውን እስከ 8 ወር ድረስ ደብቀውት እንደነበር ከመግለፅ ባለፈ በተለመደው መንገድ ነው የወለዱት ወይስ በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ (IVF or In Vitro Fertilization) ጥበብ ያሉት ነገር የለም።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከታማኝ ምንጭ ባገኘው መረጃ እናቲቱ የወለዱት በኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለትም የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ መሆኑን ተረድቷል።

ወ/ሮ መድሂን ህክምናውን ለማግኘት ወደ ህንድ ተጉዘዋል።

በዚያው ፅንሱ የ3 ወር ዕድሜ እስኪ ሞላው ድረስ ቆይተዋል።

ከሦስተኛው እስከ ወሊድ ባሉት ጊዜያት የፅንስ ክትትል በመቐለ በሚገኝ አንድ የግል ህክምና ተከታትለው በቀዶ ህክምና ለመውለድ መቻላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

በኢትዮጵያ የወሊድ ህክምና በህግ የተፈቀደው IVF / In Vitro Fertilization የህክምና ጥበብ በመቐለ ጨምሮ በአዲስ አበባ እንደሚሰጥ እየታወቀ እናቲቱ ለምን ውጭ ድረስ ለመጓዝ እንደፈለጉ የታወቀ ነገር የለም።

በ76 ዓመታቸው ልጅ ለማቀፍ የቻሉት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ እሳቸውም ልጃቸውም በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።


" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት ፤ በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን። ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ. በመስረከም 7/2019 የህንድዋ አንድህራ ፕራደሽ ግዛት ተወላጅ የሆኑት ወ/ሮ ማንጋያማ ያራማቲ በ73 ዓመታቸው በIVF ልጅ በማግኘት በእድሜ ትልቋ ተብለው ነበር።

ባለፈው ዓመት ሳፊና ናሙኩዋያ የተባሉ ኡጋንዳዊ ሴት በIVF ህክምና የመንትያ ልጆች እናት መሆን እንደቻሉ በስፋት ተዘግቦ ነበር።

እንደ አንድ የጤና መረጃ አሜሪካ ውስጥ ከሚወለዱት ህጻናት 2% የሚሆኑት በIVF, or  In Vitro Fertilization የህክምና መንገድ ሲሆን ከ8 ሚሊዮን በላይ ህፃናት በዚህ መንገድ ተወልደዋል።

NB. ኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለት የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ ነው። በላብራቶሪ ውስጥ የተፈጠረው ፅንስ በሚፈለገው ደረጃ እድገቱን ከቀጠለ በኋላ ወደ ሴቷዋ ማህፀን በማስገባት የተፈጥሮ እርግዝና ሂደቱን እንዲቀጥል የሚደረግ ይሆናል፡፡

በዚህ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ የጤና ባለሙያ ማብራሪያ ለማቅረብ ጥረት ያደርጋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94344

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The S&P 500 slumped 1.8% on Monday and Tuesday, thanks to China Evergrande, the Chinese property company that looks like it is ready to default on its more-than $300 billion in debt. Cries of the next Lehman Brothers—or maybe the next Silverado?—echoed through the canyons of Wall Street as investors prepared for the worst.

The global forecast for the Asian markets is murky following recent volatility, with crude oil prices providing support in what has been an otherwise tough month. The European markets were down and the U.S. bourses were mixed and flat and the Asian markets figure to split the difference.The TSE finished modestly lower on Friday following losses from the financial shares and property stocks.For the day, the index sank 15.09 points or 0.49 percent to finish at 3,061.35 after trading between 3,057.84 and 3,089.78. Volume was 1.39 billion shares worth 1.30 billion Singapore dollars. There were 285 decliners and 184 gainers.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA