Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከግምገማ በኋላ በደረስንበት ውጤት ነዋሪዎቹ መቶ በመቶ ጥፋተኞች ናቸው " - የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ለኮንስትራክሽን ሥራ በገቡ እና እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት አንዳንድ ሰዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች በህገወጥ መንገድ ሃይል እንዲጠቀሙ ምክንያት ሆኗል መባሉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተመዘገቡት ቆጣሪዎች…
➡️ " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " -ነዋሪዎች

🔴 " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 534 እና 535 ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር የገቡበትን ውዝግብ በሚመለከት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ በአካባቢው በመገኘት እውነታውን መመልከት እንደሚቻል ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

በዚህም መሰረት ያለውን እውነታ ለመመልከት እና ቅሬታውን ለመፍታት ከቀናት በፊት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር ፣ የሪጅኑ የህግ ክፍል፣ የጸጥታ አካላት እና ነዋሪዎች ጋር በጋራ በመሆን ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው ወቅትም የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብም በቦታው በመገኘት ከአገልግሎቱ ሃላፊዎች እና ነዋሪዎች እውነታውን ለመመልከት ጥረት አድርጓል።

አገልግሎቱ በአራብሳ የጋራ መኖሪያ መንደር ሳይት ሶስት ሃይልን ከቆጣሪ ላይ በህገወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ እንደተደረሰባቸው በመግለጽ የቆጣሪውን እዳ እንዲከፍሉ በማሳወቅ ሃይል ያቋረጠባቸው ብሎኮች 534፣ 535፣ 550 እና 551 ናቸው።

የቲክቫህ አባል ቦታው ተገኝቶ እንደተመለከተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት " በህገ-ወጥ መንገድ ቆጣሪን እንዳይቆጥር በማድረግ ሃይል ሲጠቀሙ እንደነበር ደርሼበታለሁ " በማለት ሃይል ካቋረጠባቸው አራት ብሎኮች ውስጥ ሁለቱ ማለትም ብሎክ 550 እና 551 ሃይል ተቀጥሎላቸው አገልግሎት እያገኙ ነበር።

የእነዚህ ቆጣሪዎች እዳ ባልተከፈለበት እና ከሌሎች ብሎኮች ጋር በጋራ ሃይል በተቋረጠበት ሁኔታ ለእነርሱ በማን እና በምን ሁኔታ ተቀጠለ ? የሚል ጥያቄ ለሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

ዳይሬክተሩም ፤ የቆጣሪዎቹ እዳ ባልተከፈለበት ሁኔታ የእነሱ ሃይል መጠቀም ከእርሳቸው እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተቋረጠ በኃላ በራሳቸው ሃይሉን ቀጥለው ይጠቀሙ ወይስ የአገልግሎቱ ሰው ቀጠለላቸው የሚለውን ጉዳይ ማጣራት በማድረግ " አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

በመቀጠለም ምልከታ የተደረገው ብሎክ 534 እና 535 ላይ ሲሆን እነዚህ ብሎኮች " ሃይል በህገ ወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ በኢንስፔክሽን ወቅት ተገኝተዋል " በሚል ሃይል ከተቋረጠባቸው ወር እንዳለፋቸው ተናግረዋል።

አገልግሎት በበኩሉ " ሃይሉን ያቋረጥኩት ከጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ለአንድ ዓመት ከአራት ወር በላይ ቀጥዬ ተጠቅሚያለው ያሉ እና የሚጠቀምም ስለመኖሩ በደረሰኝ ጥቆማ መሰረት ነው " ብሏል።

ነዋሪዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለው አለመጠቀማቸውን ተከራክረዋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሞያዎች ግን የቆጣሪውን ሃይል ባቋረጡበት ወቅት እነዚህ ብሎኮች መጨለማቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ሃይል በህገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል።

" ሃይል የተቋረጠብን ለብሎካችን የገባው ስሪ ፌዝ ቆጣሪ በመቆረጡ እንጂ ከተጠቀሰው ቆጣሪ ላይ ሃይል አልቀጠልንም " ሲሉ የተከራከሩት ነዋሪዎች " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።

" ከጋራ መኖሪያ ብሎኩም የተጠቀመ ቢኖር ለይቶ እነሱን ተጠያቂ ማድረግ የአገልግሎቱ ሃላፊነት ነው ሁሉም ባላጠፋው ለወር ያህል ነዋሪው ለምን ይቀጣል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

አገልግሎቱም በምላሹ " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " ቢልም ነዋሪዎች ለደህንነታቸው እንደሚሰጉ በመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅኑ ዳይሬክተር በቦታው በተገኙበት ወቅት ለነዋሪዎች መፍትሔ ለመስጠት ሃይሉን እንዲቀጠልላቸው ያደረጉ ሲሆን ለህገ ወጥ ድርጊት ምክንያት የተባለውን ቆጣሪም ከቦታው እንዲነሳ አድርገዋል።

ዳይሬክተሩ አቶ ብርሃኑ ሲጠቀሙ የነበሩትን አካላት ማንነት ከነዋሪዎቹ ወይም ኮሚቴዎቹ ማግኘት እንደሚፈልጉ እና በጊዜ ሂደት ማንነታቸውን የማጣራት ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ ሃይሉ በድጋሚ እንዲቀጠል በተደረገበት ወቅት በብሎኩ ካሉ ሁለት ቆጣሪዎች ለመታዘብ እንደተቻለው 1,500 ብር የተሞላው በ19/02/17 ዓ/ም የነበረ ቢሆንም ሃይል እስከተቋረጠበት 15/04/17 ዓም ድረስ ባለው ሁለት ወር ውስጥ ከካርዱ ጥቃም ላይ የዋለው ከ 10 ብር በታች ሆኖ ተገኝቷል።

" ቆጣሪው ሲገናኝ ያሳየው የብር መጠን 1,492. 5  አና 1,455.32 ብር ነው ይህ ማለት በ2 ወር ጊዜ ውስጥ የተጠቀሙት ከ10 ብር በታች ነው ይህ ሁሉ ህብረተሰብ በ10 ብር 2 ወር ሊጠቀም አይችልም ያማለት ቀጥታ ሲጠቀሙ እንደነበር ተጨባጭ ማስረጃ ነው " ሲሉ አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

በብሎኮች በመዟዟር በተደረገው ምልከታ በቀጥታ ያለቆጣሪ ከመስመር ላይ በመቀጠል ሃይል የሚጠቀሙ ሰዎች ስለመኖራቸው ለመታዘዘብ ተችሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/94327
Create:
Last Update:

➡️ " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " -ነዋሪዎች

🔴 " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 534 እና 535 ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር የገቡበትን ውዝግብ በሚመለከት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ በአካባቢው በመገኘት እውነታውን መመልከት እንደሚቻል ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

በዚህም መሰረት ያለውን እውነታ ለመመልከት እና ቅሬታውን ለመፍታት ከቀናት በፊት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር ፣ የሪጅኑ የህግ ክፍል፣ የጸጥታ አካላት እና ነዋሪዎች ጋር በጋራ በመሆን ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው ወቅትም የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብም በቦታው በመገኘት ከአገልግሎቱ ሃላፊዎች እና ነዋሪዎች እውነታውን ለመመልከት ጥረት አድርጓል።

አገልግሎቱ በአራብሳ የጋራ መኖሪያ መንደር ሳይት ሶስት ሃይልን ከቆጣሪ ላይ በህገወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ እንደተደረሰባቸው በመግለጽ የቆጣሪውን እዳ እንዲከፍሉ በማሳወቅ ሃይል ያቋረጠባቸው ብሎኮች 534፣ 535፣ 550 እና 551 ናቸው።

የቲክቫህ አባል ቦታው ተገኝቶ እንደተመለከተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት " በህገ-ወጥ መንገድ ቆጣሪን እንዳይቆጥር በማድረግ ሃይል ሲጠቀሙ እንደነበር ደርሼበታለሁ " በማለት ሃይል ካቋረጠባቸው አራት ብሎኮች ውስጥ ሁለቱ ማለትም ብሎክ 550 እና 551 ሃይል ተቀጥሎላቸው አገልግሎት እያገኙ ነበር።

የእነዚህ ቆጣሪዎች እዳ ባልተከፈለበት እና ከሌሎች ብሎኮች ጋር በጋራ ሃይል በተቋረጠበት ሁኔታ ለእነርሱ በማን እና በምን ሁኔታ ተቀጠለ ? የሚል ጥያቄ ለሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

ዳይሬክተሩም ፤ የቆጣሪዎቹ እዳ ባልተከፈለበት ሁኔታ የእነሱ ሃይል መጠቀም ከእርሳቸው እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተቋረጠ በኃላ በራሳቸው ሃይሉን ቀጥለው ይጠቀሙ ወይስ የአገልግሎቱ ሰው ቀጠለላቸው የሚለውን ጉዳይ ማጣራት በማድረግ " አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

በመቀጠለም ምልከታ የተደረገው ብሎክ 534 እና 535 ላይ ሲሆን እነዚህ ብሎኮች " ሃይል በህገ ወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ በኢንስፔክሽን ወቅት ተገኝተዋል " በሚል ሃይል ከተቋረጠባቸው ወር እንዳለፋቸው ተናግረዋል።

አገልግሎት በበኩሉ " ሃይሉን ያቋረጥኩት ከጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ለአንድ ዓመት ከአራት ወር በላይ ቀጥዬ ተጠቅሚያለው ያሉ እና የሚጠቀምም ስለመኖሩ በደረሰኝ ጥቆማ መሰረት ነው " ብሏል።

ነዋሪዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለው አለመጠቀማቸውን ተከራክረዋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሞያዎች ግን የቆጣሪውን ሃይል ባቋረጡበት ወቅት እነዚህ ብሎኮች መጨለማቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ሃይል በህገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል።

" ሃይል የተቋረጠብን ለብሎካችን የገባው ስሪ ፌዝ ቆጣሪ በመቆረጡ እንጂ ከተጠቀሰው ቆጣሪ ላይ ሃይል አልቀጠልንም " ሲሉ የተከራከሩት ነዋሪዎች " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።

" ከጋራ መኖሪያ ብሎኩም የተጠቀመ ቢኖር ለይቶ እነሱን ተጠያቂ ማድረግ የአገልግሎቱ ሃላፊነት ነው ሁሉም ባላጠፋው ለወር ያህል ነዋሪው ለምን ይቀጣል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

አገልግሎቱም በምላሹ " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " ቢልም ነዋሪዎች ለደህንነታቸው እንደሚሰጉ በመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅኑ ዳይሬክተር በቦታው በተገኙበት ወቅት ለነዋሪዎች መፍትሔ ለመስጠት ሃይሉን እንዲቀጠልላቸው ያደረጉ ሲሆን ለህገ ወጥ ድርጊት ምክንያት የተባለውን ቆጣሪም ከቦታው እንዲነሳ አድርገዋል።

ዳይሬክተሩ አቶ ብርሃኑ ሲጠቀሙ የነበሩትን አካላት ማንነት ከነዋሪዎቹ ወይም ኮሚቴዎቹ ማግኘት እንደሚፈልጉ እና በጊዜ ሂደት ማንነታቸውን የማጣራት ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ ሃይሉ በድጋሚ እንዲቀጠል በተደረገበት ወቅት በብሎኩ ካሉ ሁለት ቆጣሪዎች ለመታዘብ እንደተቻለው 1,500 ብር የተሞላው በ19/02/17 ዓ/ም የነበረ ቢሆንም ሃይል እስከተቋረጠበት 15/04/17 ዓም ድረስ ባለው ሁለት ወር ውስጥ ከካርዱ ጥቃም ላይ የዋለው ከ 10 ብር በታች ሆኖ ተገኝቷል።

" ቆጣሪው ሲገናኝ ያሳየው የብር መጠን 1,492. 5  አና 1,455.32 ብር ነው ይህ ማለት በ2 ወር ጊዜ ውስጥ የተጠቀሙት ከ10 ብር በታች ነው ይህ ሁሉ ህብረተሰብ በ10 ብር 2 ወር ሊጠቀም አይችልም ያማለት ቀጥታ ሲጠቀሙ እንደነበር ተጨባጭ ማስረጃ ነው " ሲሉ አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

በብሎኮች በመዟዟር በተደረገው ምልከታ በቀጥታ ያለቆጣሪ ከመስመር ላይ በመቀጠል ሃይል የሚጠቀሙ ሰዎች ስለመኖራቸው ለመታዘዘብ ተችሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA











Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/94327

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Dump Scam in Leaked Telegram Chat

A leaked Telegram discussion by 50 so-called crypto influencers has exposed the extraordinary steps they take in order to profit on the back off unsuspecting defi investors. According to a leaked screenshot of the chat, an elaborate plan to defraud defi investors using the worthless “$Few” tokens had been hatched. $Few tokens would be airdropped to some of the influencers who in turn promoted these to unsuspecting followers on Twitter.

The messaging service and social-media platform owes creditors roughly $700 million by the end of April, according to people briefed on the company’s plans and loan documents viewed by The Wall Street Journal. At the same time, Telegram Group Inc. must cover rising equipment and bandwidth expenses because of its rapid growth, despite going years without attempting to generate revenue.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA