የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ ? የመንጣቱስ ምክንያት ምንድን ነው ?
በአስደናቂነቱ ፣ በታሪካዊነቱና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በአራት አስርት ዓመታት በፊት በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው።
በእርጅናም የህልውና ስጋት እንደገጠመውም ሲነገር ነበር።
የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።
ታሪካዊው ሽሯሟ ቀለም ያለው የፋሲል ግንብ ቀለሙ ነጥቶ መታየቱ ለበርካታ መላምት ክፍት እንዲሆን አድርጎታል።
የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።
አንዳንዶች " ቅርሱ በአግባቡ አልታደሰም፤ የታወቅበትን ታሪካዊነቱንና ቀለሙንም እንዲያጣ ተደርጓል " ብለዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ምን አሉ ?
" የፋሲል ግንብ ህንጻ ሲገነባ በአነስተኛ ድንጋዮች እና በኖራ ሲሆን፣ ለረጅም ዓመታት ዝናብ፣ በፀሐይ እና በተፈጥሯዊ ሂደቶች ውስጥ ሲያልፍ በርካቶች የሚያውቁትን ይሄንን ' ሽሯማ ' መልክ አምጥቷል።
አሁን እድሳቱ የተደረገበት ኖራ አዲስ በመሆኑ ቀለሙ ነጣ ብሏል።
የእድሳት ሥራው የተከናወነው የፋሲል ግንብ በመጀመሪያ በተገነባበት ማቴሪያል (ቁስ) በዋናነት በኖራ እና በድንጋይ ነው።
የቅርስ አጠባበቅ ሕግን በተከተለ መልክ ነው የተሠራው።
የኖራው አዲስ መሆን ብቻ ይሄንን ነጣ ያለ ቀለም አምጥቷል። የኖራ እና የድንጋይ መልኩ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ወደ ድሮው መልኩ ይመለሳል።
ልዩነቱ አዲስ የመሆን እና የማርጀት ጉዳይ ነው።
የፋሲል ግንብ መጀመሪያ ሲሠራ ኖራው ለብዙ ወራት ወይም ለዓመታት ተቀብሮ የነበረ ነው አሁንም ሲታደስ መነሻውን ተከትሎ ኖራው ለበርካታ ጊዜያት እንዲቀበር ተደርጎ ጥገናው ተካሂዷል።
ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በፀሐይ፣ በዝናብ፣ በአቧራ ምክንያት በዓመታት ቀለማቸው እየተቀየረ የሚሄድ ነው ፤ ይሄኛውም ከዓመታት በኋላ የሚታወቀውን ቀለም ይይዛል።
በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥገና ሕግ መሠረት ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በተሠራበት ቁስ (ማቴሪያል) ታድሷል ወይ ? የሚለው ነው በተሠራበት ድንጋይ እና ኖራ መልሶ መጠገኑ ዋናው ነገር ነው።
ይህንንም በትክክል መሥራቱን አረጋግጠናል።
በአንዳንድ ሁኔታዎች የድሮ ቀለሙን ለማምጣት ለመልክ ሲባል ኬሚካል ይቀላቀላ እነዚህ ግን ኬሚካል ነክ ነገሮች ስለሆኑ ያልታሰበ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።
ቀለሙ እንደ ድሮው ቢመስል እንወድ ነበር፤ ሆኖም ለቀለም ተብለው የሚጨመሩ ነገሮች ያልታሰበ አደጋን በቅርስ ላይ ያመጣሉ።
በዓለም የቅርስ አጠባበቅ ደረጃ ዋነኛው ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የመነሻ ሃሳቡ ነው። ኖራው ትክክለኛ እና አስተማማኝ በመሆኑ የጥንቱ እንደያዘ የጥገና እድሳቱ እየተከናወነ ነው።
መነሻውን ሳይለቅ ጥርሳችንን ነክሰን የሠራንበት ነው።
የቀደመ መልኩ በጊዜ ብዛት ይመጣል የነበረው ገጽታ በጊዜ ሂደት ይመለሳል።
በሽሯሟ መልኩ የሚታወቀው የፋሲል ግንብ መቼ ተመልሶ ይመጣ ይሆን ? የሚለው ዝናብ ሲመታው እና የአየር ሁኔታዎች ሲፈራረቁበት እየተቀየረ ይሄዳል።
ህንጻው ወደ ቀደመ ቀለሙ ለመመለስም ከሦስት እስከ አራት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል።
አንዳንድ ቦታ ላይ በጣም የጠቋቆሩ የግንቡ አናት ላይ አካላት ነበሩ። ድንጋዮቹ ወደ ነበሩበት ለመመለስ እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚደርስ ወይም የግንቡ አናት ላይ ያሉትን ጠቆር ያሉትን የቀደመ ገጽታ ለማምጣት ከዚያ ረዘም ያለ ጊዜ ይወስዳል " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
በአስደናቂነቱ ፣ በታሪካዊነቱና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በአራት አስርት ዓመታት በፊት በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው።
በእርጅናም የህልውና ስጋት እንደገጠመውም ሲነገር ነበር።
የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።
ታሪካዊው ሽሯሟ ቀለም ያለው የፋሲል ግንብ ቀለሙ ነጥቶ መታየቱ ለበርካታ መላምት ክፍት እንዲሆን አድርጎታል።
የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።
አንዳንዶች " ቅርሱ በአግባቡ አልታደሰም፤ የታወቅበትን ታሪካዊነቱንና ቀለሙንም እንዲያጣ ተደርጓል " ብለዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ምን አሉ ?
" የፋሲል ግንብ ህንጻ ሲገነባ በአነስተኛ ድንጋዮች እና በኖራ ሲሆን፣ ለረጅም ዓመታት ዝናብ፣ በፀሐይ እና በተፈጥሯዊ ሂደቶች ውስጥ ሲያልፍ በርካቶች የሚያውቁትን ይሄንን ' ሽሯማ ' መልክ አምጥቷል።
አሁን እድሳቱ የተደረገበት ኖራ አዲስ በመሆኑ ቀለሙ ነጣ ብሏል።
የእድሳት ሥራው የተከናወነው የፋሲል ግንብ በመጀመሪያ በተገነባበት ማቴሪያል (ቁስ) በዋናነት በኖራ እና በድንጋይ ነው።
የቅርስ አጠባበቅ ሕግን በተከተለ መልክ ነው የተሠራው።
የኖራው አዲስ መሆን ብቻ ይሄንን ነጣ ያለ ቀለም አምጥቷል። የኖራ እና የድንጋይ መልኩ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ወደ ድሮው መልኩ ይመለሳል።
ልዩነቱ አዲስ የመሆን እና የማርጀት ጉዳይ ነው።
የፋሲል ግንብ መጀመሪያ ሲሠራ ኖራው ለብዙ ወራት ወይም ለዓመታት ተቀብሮ የነበረ ነው አሁንም ሲታደስ መነሻውን ተከትሎ ኖራው ለበርካታ ጊዜያት እንዲቀበር ተደርጎ ጥገናው ተካሂዷል።
ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በፀሐይ፣ በዝናብ፣ በአቧራ ምክንያት በዓመታት ቀለማቸው እየተቀየረ የሚሄድ ነው ፤ ይሄኛውም ከዓመታት በኋላ የሚታወቀውን ቀለም ይይዛል።
በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥገና ሕግ መሠረት ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በተሠራበት ቁስ (ማቴሪያል) ታድሷል ወይ ? የሚለው ነው በተሠራበት ድንጋይ እና ኖራ መልሶ መጠገኑ ዋናው ነገር ነው።
ይህንንም በትክክል መሥራቱን አረጋግጠናል።
በአንዳንድ ሁኔታዎች የድሮ ቀለሙን ለማምጣት ለመልክ ሲባል ኬሚካል ይቀላቀላ እነዚህ ግን ኬሚካል ነክ ነገሮች ስለሆኑ ያልታሰበ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።
ቀለሙ እንደ ድሮው ቢመስል እንወድ ነበር፤ ሆኖም ለቀለም ተብለው የሚጨመሩ ነገሮች ያልታሰበ አደጋን በቅርስ ላይ ያመጣሉ።
በዓለም የቅርስ አጠባበቅ ደረጃ ዋነኛው ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የመነሻ ሃሳቡ ነው። ኖራው ትክክለኛ እና አስተማማኝ በመሆኑ የጥንቱ እንደያዘ የጥገና እድሳቱ እየተከናወነ ነው።
መነሻውን ሳይለቅ ጥርሳችንን ነክሰን የሠራንበት ነው።
የቀደመ መልኩ በጊዜ ብዛት ይመጣል የነበረው ገጽታ በጊዜ ሂደት ይመለሳል።
በሽሯሟ መልኩ የሚታወቀው የፋሲል ግንብ መቼ ተመልሶ ይመጣ ይሆን ? የሚለው ዝናብ ሲመታው እና የአየር ሁኔታዎች ሲፈራረቁበት እየተቀየረ ይሄዳል።
ህንጻው ወደ ቀደመ ቀለሙ ለመመለስም ከሦስት እስከ አራት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል።
አንዳንድ ቦታ ላይ በጣም የጠቋቆሩ የግንቡ አናት ላይ አካላት ነበሩ። ድንጋዮቹ ወደ ነበሩበት ለመመለስ እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚደርስ ወይም የግንቡ አናት ላይ ያሉትን ጠቆር ያሉትን የቀደመ ገጽታ ለማምጣት ከዚያ ረዘም ያለ ጊዜ ይወስዳል " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/93788
Create:
Last Update:
Last Update:
የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ ? የመንጣቱስ ምክንያት ምንድን ነው ?
በአስደናቂነቱ ፣ በታሪካዊነቱና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በአራት አስርት ዓመታት በፊት በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው።
በእርጅናም የህልውና ስጋት እንደገጠመውም ሲነገር ነበር።
የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።
ታሪካዊው ሽሯሟ ቀለም ያለው የፋሲል ግንብ ቀለሙ ነጥቶ መታየቱ ለበርካታ መላምት ክፍት እንዲሆን አድርጎታል።
የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።
አንዳንዶች " ቅርሱ በአግባቡ አልታደሰም፤ የታወቅበትን ታሪካዊነቱንና ቀለሙንም እንዲያጣ ተደርጓል " ብለዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ምን አሉ ?
" የፋሲል ግንብ ህንጻ ሲገነባ በአነስተኛ ድንጋዮች እና በኖራ ሲሆን፣ ለረጅም ዓመታት ዝናብ፣ በፀሐይ እና በተፈጥሯዊ ሂደቶች ውስጥ ሲያልፍ በርካቶች የሚያውቁትን ይሄንን ' ሽሯማ ' መልክ አምጥቷል።
አሁን እድሳቱ የተደረገበት ኖራ አዲስ በመሆኑ ቀለሙ ነጣ ብሏል።
የእድሳት ሥራው የተከናወነው የፋሲል ግንብ በመጀመሪያ በተገነባበት ማቴሪያል (ቁስ) በዋናነት በኖራ እና በድንጋይ ነው።
የቅርስ አጠባበቅ ሕግን በተከተለ መልክ ነው የተሠራው።
የኖራው አዲስ መሆን ብቻ ይሄንን ነጣ ያለ ቀለም አምጥቷል። የኖራ እና የድንጋይ መልኩ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ወደ ድሮው መልኩ ይመለሳል።
ልዩነቱ አዲስ የመሆን እና የማርጀት ጉዳይ ነው።
የፋሲል ግንብ መጀመሪያ ሲሠራ ኖራው ለብዙ ወራት ወይም ለዓመታት ተቀብሮ የነበረ ነው አሁንም ሲታደስ መነሻውን ተከትሎ ኖራው ለበርካታ ጊዜያት እንዲቀበር ተደርጎ ጥገናው ተካሂዷል።
ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በፀሐይ፣ በዝናብ፣ በአቧራ ምክንያት በዓመታት ቀለማቸው እየተቀየረ የሚሄድ ነው ፤ ይሄኛውም ከዓመታት በኋላ የሚታወቀውን ቀለም ይይዛል።
በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥገና ሕግ መሠረት ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በተሠራበት ቁስ (ማቴሪያል) ታድሷል ወይ ? የሚለው ነው በተሠራበት ድንጋይ እና ኖራ መልሶ መጠገኑ ዋናው ነገር ነው።
ይህንንም በትክክል መሥራቱን አረጋግጠናል።
በአንዳንድ ሁኔታዎች የድሮ ቀለሙን ለማምጣት ለመልክ ሲባል ኬሚካል ይቀላቀላ እነዚህ ግን ኬሚካል ነክ ነገሮች ስለሆኑ ያልታሰበ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።
ቀለሙ እንደ ድሮው ቢመስል እንወድ ነበር፤ ሆኖም ለቀለም ተብለው የሚጨመሩ ነገሮች ያልታሰበ አደጋን በቅርስ ላይ ያመጣሉ።
በዓለም የቅርስ አጠባበቅ ደረጃ ዋነኛው ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የመነሻ ሃሳቡ ነው። ኖራው ትክክለኛ እና አስተማማኝ በመሆኑ የጥንቱ እንደያዘ የጥገና እድሳቱ እየተከናወነ ነው።
መነሻውን ሳይለቅ ጥርሳችንን ነክሰን የሠራንበት ነው።
የቀደመ መልኩ በጊዜ ብዛት ይመጣል የነበረው ገጽታ በጊዜ ሂደት ይመለሳል።
በሽሯሟ መልኩ የሚታወቀው የፋሲል ግንብ መቼ ተመልሶ ይመጣ ይሆን ? የሚለው ዝናብ ሲመታው እና የአየር ሁኔታዎች ሲፈራረቁበት እየተቀየረ ይሄዳል።
ህንጻው ወደ ቀደመ ቀለሙ ለመመለስም ከሦስት እስከ አራት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል።
አንዳንድ ቦታ ላይ በጣም የጠቋቆሩ የግንቡ አናት ላይ አካላት ነበሩ። ድንጋዮቹ ወደ ነበሩበት ለመመለስ እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚደርስ ወይም የግንቡ አናት ላይ ያሉትን ጠቆር ያሉትን የቀደመ ገጽታ ለማምጣት ከዚያ ረዘም ያለ ጊዜ ይወስዳል " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
በአስደናቂነቱ ፣ በታሪካዊነቱና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በአራት አስርት ዓመታት በፊት በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው።
በእርጅናም የህልውና ስጋት እንደገጠመውም ሲነገር ነበር።
የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።
ታሪካዊው ሽሯሟ ቀለም ያለው የፋሲል ግንብ ቀለሙ ነጥቶ መታየቱ ለበርካታ መላምት ክፍት እንዲሆን አድርጎታል።
የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።
አንዳንዶች " ቅርሱ በአግባቡ አልታደሰም፤ የታወቅበትን ታሪካዊነቱንና ቀለሙንም እንዲያጣ ተደርጓል " ብለዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ምን አሉ ?
" የፋሲል ግንብ ህንጻ ሲገነባ በአነስተኛ ድንጋዮች እና በኖራ ሲሆን፣ ለረጅም ዓመታት ዝናብ፣ በፀሐይ እና በተፈጥሯዊ ሂደቶች ውስጥ ሲያልፍ በርካቶች የሚያውቁትን ይሄንን ' ሽሯማ ' መልክ አምጥቷል።
አሁን እድሳቱ የተደረገበት ኖራ አዲስ በመሆኑ ቀለሙ ነጣ ብሏል።
የእድሳት ሥራው የተከናወነው የፋሲል ግንብ በመጀመሪያ በተገነባበት ማቴሪያል (ቁስ) በዋናነት በኖራ እና በድንጋይ ነው።
የቅርስ አጠባበቅ ሕግን በተከተለ መልክ ነው የተሠራው።
የኖራው አዲስ መሆን ብቻ ይሄንን ነጣ ያለ ቀለም አምጥቷል። የኖራ እና የድንጋይ መልኩ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ወደ ድሮው መልኩ ይመለሳል።
ልዩነቱ አዲስ የመሆን እና የማርጀት ጉዳይ ነው።
የፋሲል ግንብ መጀመሪያ ሲሠራ ኖራው ለብዙ ወራት ወይም ለዓመታት ተቀብሮ የነበረ ነው አሁንም ሲታደስ መነሻውን ተከትሎ ኖራው ለበርካታ ጊዜያት እንዲቀበር ተደርጎ ጥገናው ተካሂዷል።
ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በፀሐይ፣ በዝናብ፣ በአቧራ ምክንያት በዓመታት ቀለማቸው እየተቀየረ የሚሄድ ነው ፤ ይሄኛውም ከዓመታት በኋላ የሚታወቀውን ቀለም ይይዛል።
በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥገና ሕግ መሠረት ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በተሠራበት ቁስ (ማቴሪያል) ታድሷል ወይ ? የሚለው ነው በተሠራበት ድንጋይ እና ኖራ መልሶ መጠገኑ ዋናው ነገር ነው።
ይህንንም በትክክል መሥራቱን አረጋግጠናል።
በአንዳንድ ሁኔታዎች የድሮ ቀለሙን ለማምጣት ለመልክ ሲባል ኬሚካል ይቀላቀላ እነዚህ ግን ኬሚካል ነክ ነገሮች ስለሆኑ ያልታሰበ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።
ቀለሙ እንደ ድሮው ቢመስል እንወድ ነበር፤ ሆኖም ለቀለም ተብለው የሚጨመሩ ነገሮች ያልታሰበ አደጋን በቅርስ ላይ ያመጣሉ።
በዓለም የቅርስ አጠባበቅ ደረጃ ዋነኛው ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የመነሻ ሃሳቡ ነው። ኖራው ትክክለኛ እና አስተማማኝ በመሆኑ የጥንቱ እንደያዘ የጥገና እድሳቱ እየተከናወነ ነው።
መነሻውን ሳይለቅ ጥርሳችንን ነክሰን የሠራንበት ነው።
የቀደመ መልኩ በጊዜ ብዛት ይመጣል የነበረው ገጽታ በጊዜ ሂደት ይመለሳል።
በሽሯሟ መልኩ የሚታወቀው የፋሲል ግንብ መቼ ተመልሶ ይመጣ ይሆን ? የሚለው ዝናብ ሲመታው እና የአየር ሁኔታዎች ሲፈራረቁበት እየተቀየረ ይሄዳል።
ህንጻው ወደ ቀደመ ቀለሙ ለመመለስም ከሦስት እስከ አራት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል።
አንዳንድ ቦታ ላይ በጣም የጠቋቆሩ የግንቡ አናት ላይ አካላት ነበሩ። ድንጋዮቹ ወደ ነበሩበት ለመመለስ እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚደርስ ወይም የግንቡ አናት ላይ ያሉትን ጠቆር ያሉትን የቀደመ ገጽታ ለማምጣት ከዚያ ረዘም ያለ ጊዜ ይወስዳል " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA




Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93788