Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93770-93771-93772-93773-93774-93775-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93770 -
Telegram Group & Telegram Channel
" የሀገር ሀብትና የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉ የቡና ምርት በቀልጣፋ አገልግሎት እጦት ለጥራት ችግር እየተዳረገብን ነዉ " - የቡና አቅራቢዎች

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርመራና ሰርትፊኬሽን ማዕከል በሀገራች ከፍተኛ ቡና አምራች ከሚባሉ ሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ ሻኪሶ ፣ ቡሌሆራ እና አማሮ አከባቢዎች የሚገኙ ምርቶች የጥራት ልኬት እና ሰርትፊኬሽን አግኝተዉ ቡናን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚቀርቡበት ማዕከል ነው።

በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሀዋሳ ከተማ ተቋሙ ከሚገኝበት የቀድሞዉ የደቡብ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ ዙሪያ በአራቱም አቅጣጫ ቡና የጫኑ በርካታ ተሸከርካሪዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምክንያቱን ለማጣራት ክትትል አድርጓል።

የቡና አቅራቢዎች እና አሽከርካሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ ባለዉ የወረፋ ብዛትና ተያያዥ ችግሮች ላላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸዉንና አልፎም ለሀገር ትልቅ የገቢ ምንጭ በሆነዉ የቡና ምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል።

" ቡና በባህሪው እንደ ሙሽራ እንክብካቤ ይፈልጋል " ያሉን አንድ የቡና ላኪ " በቦታዉ ባለዉ ወረፋ መብዛትና ተገቢነት በለሌዉ የተሽከርካሪ አቋቋም ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረግን ነዉ " ብለዋል።

" በማዕከሉ ዙሪያ ተሰልፈን አምስትና ስድስት ቀናትና አለፍ ሲልም ከዛም በላይ አስር ቀን የመቆየት ሁኔታዎች አሉ " ያሉን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ የቡና አቅራቢ " ቡና ሳይወጋ በሻራ ዉስጥ ታፍኖ ለረጅም ቀናት ስለሚቆይ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በሚናቀርብበት ወቅት የጥራት ደረጃ መዉረድና በከፍተኛ ሁኔታ የኪሎግራም መቀነስ እያጋጠመን ነዉ " ብለዋል።

" ቀልጣፋ አገልግሎት ባለማግኘታችን በእኛና በተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም በቡና አቅራቢዎች እና ጉዳይ አስፈፃሚዎች መካከል አለመተማመኖች እየተፈጠሩ ነዉ " ያሉን አሽከርካሪዎች " ለፓርኪንግ፣ ምግብ ፣ አልጋ መሰል አላስፈላጊ ወጪዎችን እያወጣን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ቡና በሀገር ደረጃ ባለዉ ከፍተኛ የገቢ ምንጭነት ልክ ትኩረት አልተሰጠውም " የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ " ፈጣን መፍትሔ ካልተበጀለት ጉዳቱ ከኛ አልፎ አምራች አርሶአደሮች፣ ሰፊ የስራ ዕድል በተፈጠረላቸው ወጣቶችና በሀገር የዉጪ ምንዛሪ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩ አይቀርም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ስሜን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ የዘንድሮ የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ቀደም ሲል ከነበረዉ የቦታ ጥበትና ተያያዥ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ አለመሆን ዋነኛ ምክንያት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

የችግሩን አሳሳብነትና የቡናን ሀገራዊ ጥቅሙን በመግለፅ ለሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ምላሽም እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ የቡና ምርቶች ወደ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት አስፈላጊዉ የእርጥበት መጠን ላይ ሳይደርሱ የሚመጡበት አጋጣሚዎች ስላሉ ተገቢዉ የእርጥበት መጠናቸዉ ላይ እስኪደርሱ ድረስ መወጋትም ሆነ የቅምሻ ልኬት ስለማይደረግላቸዉና ለኮንትሮባንድ እንዳይጋለጡ ሲባል ወደ ኋላ ስለማይመለሱ በማዕከሉ እንዲቆዩ ስለሚደረግ የተሽከርካሪዎች ክምችት እንደሚፋጠርም አስታውቀዋል።

ማዕከሉ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ ክልል ቡና አምራች አከባቢዎች አገልግሎት የሚሰጥና የሀገራችንን ዋነኛ የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የሲዳማ ክልል መንግስትና ተጠሪ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ መፍትሔ ቢሰጡ ጥሩ ነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬን አነጋግሯል።

" ቡና ለሲዳማ ክልል ልዩ ትርጉም ያለዉ የገቢ ምንጭና የክልሉም መለያም ጭምር ነዉ " ያሉ ሲሆን በ2017 ዓ/ም ብቻ ከክልሉ ከ37 ሺ ቶን በላይ ቡና መሰብሰቡን ገልፀዉ በዘንድሮዉ ሀገር አቀፍ የቡና ቅምሻ ወድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰሌንስ) ከ1ኛ እስከ 39ኛ ድረስ የወጡት የክልሉ አምራች አርሶ አደሮች መሆናቸውን አስታዉቀዋል።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ያለበትን ጫና የክልሉ መንግስት መረዳቱንና በአጭር ጊዜ ዉስጥ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/93770
Create:
Last Update:

" የሀገር ሀብትና የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉ የቡና ምርት በቀልጣፋ አገልግሎት እጦት ለጥራት ችግር እየተዳረገብን ነዉ " - የቡና አቅራቢዎች

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርመራና ሰርትፊኬሽን ማዕከል በሀገራች ከፍተኛ ቡና አምራች ከሚባሉ ሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ ሻኪሶ ፣ ቡሌሆራ እና አማሮ አከባቢዎች የሚገኙ ምርቶች የጥራት ልኬት እና ሰርትፊኬሽን አግኝተዉ ቡናን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚቀርቡበት ማዕከል ነው።

በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሀዋሳ ከተማ ተቋሙ ከሚገኝበት የቀድሞዉ የደቡብ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ ዙሪያ በአራቱም አቅጣጫ ቡና የጫኑ በርካታ ተሸከርካሪዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምክንያቱን ለማጣራት ክትትል አድርጓል።

የቡና አቅራቢዎች እና አሽከርካሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ ባለዉ የወረፋ ብዛትና ተያያዥ ችግሮች ላላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸዉንና አልፎም ለሀገር ትልቅ የገቢ ምንጭ በሆነዉ የቡና ምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል።

" ቡና በባህሪው እንደ ሙሽራ እንክብካቤ ይፈልጋል " ያሉን አንድ የቡና ላኪ " በቦታዉ ባለዉ ወረፋ መብዛትና ተገቢነት በለሌዉ የተሽከርካሪ አቋቋም ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረግን ነዉ " ብለዋል።

" በማዕከሉ ዙሪያ ተሰልፈን አምስትና ስድስት ቀናትና አለፍ ሲልም ከዛም በላይ አስር ቀን የመቆየት ሁኔታዎች አሉ " ያሉን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ የቡና አቅራቢ " ቡና ሳይወጋ በሻራ ዉስጥ ታፍኖ ለረጅም ቀናት ስለሚቆይ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በሚናቀርብበት ወቅት የጥራት ደረጃ መዉረድና በከፍተኛ ሁኔታ የኪሎግራም መቀነስ እያጋጠመን ነዉ " ብለዋል።

" ቀልጣፋ አገልግሎት ባለማግኘታችን በእኛና በተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም በቡና አቅራቢዎች እና ጉዳይ አስፈፃሚዎች መካከል አለመተማመኖች እየተፈጠሩ ነዉ " ያሉን አሽከርካሪዎች " ለፓርኪንግ፣ ምግብ ፣ አልጋ መሰል አላስፈላጊ ወጪዎችን እያወጣን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ቡና በሀገር ደረጃ ባለዉ ከፍተኛ የገቢ ምንጭነት ልክ ትኩረት አልተሰጠውም " የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ " ፈጣን መፍትሔ ካልተበጀለት ጉዳቱ ከኛ አልፎ አምራች አርሶአደሮች፣ ሰፊ የስራ ዕድል በተፈጠረላቸው ወጣቶችና በሀገር የዉጪ ምንዛሪ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩ አይቀርም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ስሜን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ የዘንድሮ የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ቀደም ሲል ከነበረዉ የቦታ ጥበትና ተያያዥ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ አለመሆን ዋነኛ ምክንያት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

የችግሩን አሳሳብነትና የቡናን ሀገራዊ ጥቅሙን በመግለፅ ለሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ምላሽም እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ የቡና ምርቶች ወደ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት አስፈላጊዉ የእርጥበት መጠን ላይ ሳይደርሱ የሚመጡበት አጋጣሚዎች ስላሉ ተገቢዉ የእርጥበት መጠናቸዉ ላይ እስኪደርሱ ድረስ መወጋትም ሆነ የቅምሻ ልኬት ስለማይደረግላቸዉና ለኮንትሮባንድ እንዳይጋለጡ ሲባል ወደ ኋላ ስለማይመለሱ በማዕከሉ እንዲቆዩ ስለሚደረግ የተሽከርካሪዎች ክምችት እንደሚፋጠርም አስታውቀዋል።

ማዕከሉ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ ክልል ቡና አምራች አከባቢዎች አገልግሎት የሚሰጥና የሀገራችንን ዋነኛ የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የሲዳማ ክልል መንግስትና ተጠሪ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ መፍትሔ ቢሰጡ ጥሩ ነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬን አነጋግሯል።

" ቡና ለሲዳማ ክልል ልዩ ትርጉም ያለዉ የገቢ ምንጭና የክልሉም መለያም ጭምር ነዉ " ያሉ ሲሆን በ2017 ዓ/ም ብቻ ከክልሉ ከ37 ሺ ቶን በላይ ቡና መሰብሰቡን ገልፀዉ በዘንድሮዉ ሀገር አቀፍ የቡና ቅምሻ ወድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰሌንስ) ከ1ኛ እስከ 39ኛ ድረስ የወጡት የክልሉ አምራች አርሶ አደሮች መሆናቸውን አስታዉቀዋል።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ያለበትን ጫና የክልሉ መንግስት መረዳቱንና በአጭር ጊዜ ዉስጥ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93770

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

The messaging service and social-media platform owes creditors roughly $700 million by the end of April, according to people briefed on the company’s plans and loan documents viewed by The Wall Street Journal. At the same time, Telegram Group Inc. must cover rising equipment and bandwidth expenses because of its rapid growth, despite going years without attempting to generate revenue.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA