Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ እርምጃ እንወሰወዳለን "  - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሴት ሙስሊም ተማሪዎች #ሒጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላና የመብት ጥሰት አስመልክቶ ዛሬ ዓርብ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል። በዚሁ መግለጫ " የፌደራል…
#Update

" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃዎችን እንስወዳለን "   - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ከሃይማኖታዊ ስርዓት ውጪ በሆነ ሁኔታ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላ እና የመብት ጥሰት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ የተከለከሉ 160 የያዝነው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዲፈታ ካለፈው ጥቅምት 2017 ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች እንዳደረገ ምክር ቤቱ ጠቅሷል።

ትምህርት ቤቱ በያዝነው ሳምንት የትግራይ ትምህርት ቢሮ አዲስ ህግ እና ደንብ ባልወጣበት ሁኔታ ተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸው እንዳይማሩ መደረጉ ልክ እንዳልሆነ አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ባለመቀበል ተማሪዎቹ በማስፈራራት እና በማሰር ከእውቀት ገበታ ውጭ እንዲሆኑ ማድረጉ ምክር ቤቱ በመግለጫው አስታውቋል።

ምክር ቤት ባወጣው የ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ፦

1. የሂጃብ ክልከላው በህገ-መንግስት የተቀመጡ የጋራ እና የግል መብቶች የሚፃረር ፣ በትምህርት ሚንስቴር እና በክልሉ መከበር ያለባቸው ደንቦች የጣሰ ነው።

2. የትምህርት ቤቶች ህግ በህገ-መንግስቱ የተቀመጡ መብቶች የሚፃረር መሆን የለበትም። በትምህርት ሚንስቴር ደንብ ቁጥር -6 ንኡስ ቁጥር -3 ሂጃብ መልበስ እንደሚፈቅድ በግልፅ ተደንግጓል ስለሆነም ጥያቄያችን በዚሁ ደንብ በአስቸኳይ እንዲመለስ እንጠይቃለን።

3. ትግራይ አሁን ባለችበት ፓለቲካዊ ቀውስ በሃይማኖት ምክንያት ሌላ ቀውስ መጨመር ተገቢ ስላልሆነ ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስልን።

4. በጦርነቱ ምክንያት ከእውቀት መአድ ርቀው የነበሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንዲበረታቱ የሚገባቸው ሙስሊም ሴቶች ማበረታታት ሲገባ ሂጃብ በመልበሳቸው ብቻ ከትምህርት ገበታ መከልከል ፍፁም ኢ-ህጋዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንጠይቃለን።

5. ጉዳዩ በማንኛውም መልኩ ለፓለቲካ ፍጆታ መጠቀምያ ማዋል ስለማይገባ ጉዳዩ እንዳይፈታ የሚያወሳስቡት ግለሰቦች ወይም አካላት መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርጋቸው ጥሪ እናቀርባለን።

6. ኢ-ህገመንግስታዊ  ተግባሩን የሌሎች እምነት ተከታዮች እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች እንዲያወግዙት ጥሪ እናቀርባለን።

7. ከትምህርት ገበታ የተስተጓጎሉት ተማሪዎች የትምህርት ሚንስቴር ያወጣው ሁሉም ትምህርት ቤቶች መፈፀም የሚገባቸው የአለባበስ ሁኔታ የሚመለከት ህግና ደንብ ያልጣሱ ስለሆነ ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ እንዲደረግ በአፅንኦት እንጠይቃለን።

8. ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ እየተደረገ ያለው ተግባር ሰብአዊ መብቶች ፣ ክልላዊ ፣ አገራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ህጎች የሚፃረር በመሆኑ በጥብቅ እንኮንነዋለን።

9. ከትምህርት ሚንስቴር መመሪያ እና ደንብ ባፈነገጠ መልኩ በግል ፍላጎት ብቻ በመመራት በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ህገ-ወጥ ተግባር የፈፀሙት ግለሰቦች እና አካላት በህግ እንዲጠየቁ ጥሪ እናቀርባለን።

10. የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ህገ-ወጥ ተግባር እንዲወገዝ ድጋፍ የቸራችሁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል።

11. ፍትሃዊ ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የክልላችን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር በመምከር በቀጣይ የምንወስዳቸው ሰላማዊ የትግል እርምጃዎች ለህዝባችን እናሳውቃለን።

... ብሏል።

መረጃውን የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia 



tg-me.com/tikvahethiopia/93382
Create:
Last Update:

#Update

" ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ ቀጣይ ሰላማዊ እርምጃዎችን እንስወዳለን "   - የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ከሃይማኖታዊ ስርዓት ውጪ በሆነ ሁኔታ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላ እና የመብት ጥሰት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በአክሱም ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ የተከለከሉ 160 የያዝነው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዲፈታ ካለፈው ጥቅምት 2017 ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች እንዳደረገ ምክር ቤቱ ጠቅሷል።

ትምህርት ቤቱ በያዝነው ሳምንት የትግራይ ትምህርት ቢሮ አዲስ ህግ እና ደንብ ባልወጣበት ሁኔታ ተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸው እንዳይማሩ መደረጉ ልክ እንዳልሆነ አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ ባለመቀበል ተማሪዎቹ በማስፈራራት እና በማሰር ከእውቀት ገበታ ውጭ እንዲሆኑ ማድረጉ ምክር ቤቱ በመግለጫው አስታውቋል።

ምክር ቤት ባወጣው የ11 ነጥብ የአቋም መግለጫ፦

1. የሂጃብ ክልከላው በህገ-መንግስት የተቀመጡ የጋራ እና የግል መብቶች የሚፃረር ፣ በትምህርት ሚንስቴር እና በክልሉ መከበር ያለባቸው ደንቦች የጣሰ ነው።

2. የትምህርት ቤቶች ህግ በህገ-መንግስቱ የተቀመጡ መብቶች የሚፃረር መሆን የለበትም። በትምህርት ሚንስቴር ደንብ ቁጥር -6 ንኡስ ቁጥር -3 ሂጃብ መልበስ እንደሚፈቅድ በግልፅ ተደንግጓል ስለሆነም ጥያቄያችን በዚሁ ደንብ በአስቸኳይ እንዲመለስ እንጠይቃለን።

3. ትግራይ አሁን ባለችበት ፓለቲካዊ ቀውስ በሃይማኖት ምክንያት ሌላ ቀውስ መጨመር ተገቢ ስላልሆነ ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስልን።

4. በጦርነቱ ምክንያት ከእውቀት መአድ ርቀው የነበሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ እንዲበረታቱ የሚገባቸው ሙስሊም ሴቶች ማበረታታት ሲገባ ሂጃብ በመልበሳቸው ብቻ ከትምህርት ገበታ መከልከል ፍፁም ኢ-ህጋዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንጠይቃለን።

5. ጉዳዩ በማንኛውም መልኩ ለፓለቲካ ፍጆታ መጠቀምያ ማዋል ስለማይገባ ጉዳዩ እንዳይፈታ የሚያወሳስቡት ግለሰቦች ወይም አካላት መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርጋቸው ጥሪ እናቀርባለን።

6. ኢ-ህገመንግስታዊ  ተግባሩን የሌሎች እምነት ተከታዮች እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች እንዲያወግዙት ጥሪ እናቀርባለን።

7. ከትምህርት ገበታ የተስተጓጎሉት ተማሪዎች የትምህርት ሚንስቴር ያወጣው ሁሉም ትምህርት ቤቶች መፈፀም የሚገባቸው የአለባበስ ሁኔታ የሚመለከት ህግና ደንብ ያልጣሱ ስለሆነ ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ እንዲደረግ በአፅንኦት እንጠይቃለን።

8. ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ እየተደረገ ያለው ተግባር ሰብአዊ መብቶች ፣ ክልላዊ ፣ አገራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ህጎች የሚፃረር በመሆኑ በጥብቅ እንኮንነዋለን።

9. ከትምህርት ሚንስቴር መመሪያ እና ደንብ ባፈነገጠ መልኩ በግል ፍላጎት ብቻ በመመራት በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ህገ-ወጥ ተግባር የፈፀሙት ግለሰቦች እና አካላት በህግ እንዲጠየቁ ጥሪ እናቀርባለን።

10. የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ የተደረገው ህገ-ወጥ ተግባር እንዲወገዝ ድጋፍ የቸራችሁ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ምክር ቤቱ ምስጋና ያቀርባል።

11. ፍትሃዊ ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የክልላችን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር በመምከር በቀጣይ የምንወስዳቸው ሰላማዊ የትግል እርምጃዎች ለህዝባችን እናሳውቃለን።

... ብሏል።

መረጃውን የላከው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia 

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93382

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

A project of our size needs at least a few hundred million dollars per year to keep going,” Mr. Durov wrote in his public channel on Telegram late last year. “While doing that, we will remain independent and stay true to our values, redefining how a tech company should operate.

The global forecast for the Asian markets is murky following recent volatility, with crude oil prices providing support in what has been an otherwise tough month. The European markets were down and the U.S. bourses were mixed and flat and the Asian markets figure to split the difference.The TSE finished modestly lower on Friday following losses from the financial shares and property stocks.For the day, the index sank 15.09 points or 0.49 percent to finish at 3,061.35 after trading between 3,057.84 and 3,089.78. Volume was 1.39 billion shares worth 1.30 billion Singapore dollars. There were 285 decliners and 184 gainers.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA