Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
በተአምር የተፈረች ነፍስ !

" ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል" - ከቦናዉ የመኪና አደጋ የተረፈችው የኔነሽ ለገሠ


በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ከቀጠፈዉ የመኪና አደጋ የተረፉት 4 ሰዎች ብቻ ናቸው።

ከእነዚህ ዉስጥ ሁለቱ ገና መኪናዉ ወደ ገደል ሳይገባ ዘለዉ በመውረዳቸው መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ሁለት ሴቶች ደግሞ ተሽከርካሪዉ ወንዝ ዉስጥ ከገባ በኋላ በከፍተኛ ጉዳት በሕይወት ተርፈዉ ከቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለተሻለ ህክምና ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸዉን የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን መረጃ ያሳያል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ከዚህ አስከፊ አደጋ የተረፉትን ሁለት ሴቶች በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለመጠየቅ ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አቅንቷል።

ከአደጋው የተረፉት ሁለቱ ሴቶች ስማቸው የነኔሽ ለገሠ እና ከበቡሽ ሃይሌ ይባላሉ።

ከበቡሽ ኃይሌ በአደጋዉ ምክንያት ቀዶ ህክምና ተደርጎላት በመተንፈሻ ማሽን እርዳታ ዉስጥ ትገኛለች።

የኔነሽ ገለሠ ደግሞ በድንጋጤና ከፍተኛ ሕመም ዉስጥ ብትሆንም ማዉራት እና የተፈጠረውን አደጋ በመጠኑም ቢሆን ማስታወስና ከአስታማሚዎቿ ጋርም መግባባት ትችላለች።

ከአደጋው ስለተረፉት ሁለት ሴቶች በምን አይነት የጤንነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ማብራሪያ ከሆስፒታሉ የጠየቅን ቢሆንም ሆስፒታሉ ከአደጋው ጋር በተያያዘ " ከፖሊስ በስተቀር መረጃ ለመስጠት እንቸገራለን " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

በወቅቱ የኔነሽ ለገሰን ሲያስታምሙ ያገኘናቸው አቶ ደበበን አሁን ስላለችበት የጤና ሁኔታ ጠይቀናቸዋል።

አቶ ደበበ እንደነገሩን የኔነሽ ስለ አደጋዉ ዝርዝር ጉዳዩ እንዳልተነገራትና በዚህ ዘግናኝ አደጋ ምክንያት አንድ እህቷን እና ሁለት ወንድሞቿን ማጣቷን ነግረውናል።

በሆስፒታሉ በተገኘን ጊዜም የኔነሽ ነቃ ብላ እያወራች ነበር።

አማርኛ ቋንቋን በሚገባ መናገር ባትችልም በሲዳምኛ ቋንቋ ስለ አደጋው ስታስረዳ ማዳመጥ ችለናል።

" አደጋዉ የተከሰተዉ የአጎቴ ልጅ ሚስት ሊያገባ ስለነበር ቤተ-ዘመድ ተሰባስቦ ሙሽራዋን ለመዉሰድ ወደ ወራንቻ ቀበሌ እየሄድን በነበርንበት ወቅት ነዉ" ብላለች።

" እኔ መሃል ነበርኩ፤ ሁላችን በደስታ በዝማሬ ላይ ነበርን ወደ ዋናዉ መስመር ወጥተን ጋላና ወንዝ ስንደርስ በድንገት መኪናዉ ድልድዩን ስቶ ወደ ወንዝ መግባት ሲጀምር በጩኸት ብዛት.... " ንግግሯን መጨረሽ አልቻለችም።

ይኽን በምታወራበት ወቅት እምባ በሁለቱም ዐይኖቿ ይወርድ ነበር።

ከተወሰነ መረጋጋት በኋላ የኔነሽ ስለ አሰቃቂው አደጋ የምታስታውሰውን ማስረዳት ቀጠለች ፤ " አላዉቅም እኔ ዛሬ ነዉ ሀዋሳ መሆኔን እንኳን የተነገረኝ! ሌላዉን አላዉቅም ፤ አጎቴ አብረዉኝ ስለነበሩ አጠቃላይ ስለ ሰርገኛዉ ደጋግሜ ስጠይቀዉ 'እነሱ ቦና ናቸዉ! አንቺ ስለተጎዳሽ ነዉ እዚህ የመጣሽዉ' ይለኛል " በማለት አስታማሚዋ የነበሩት አቶ ከበደ እንደነገሩን ይኽንን መሪር ሀዘን አለመስማቷን አረጋግጣልናለች።

ይህንን በተናገረችበት ቅጽበት አጠገቧ የነበሩት ሁሉ ዝምታን መረጡ ሁሉም እንደተፈራራ ዝም ተባባለ በዚህ ጊዜ አንድ ጥያቄ ቀረበላት "ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በመትረፍሽ ምን ተሰማሽ ? " የሚል።

የኔነሽ ከነበረችበት ትካዜ በመጠኑም ነቃ ብላ " ከቦታዉ አደገኛነትና ከነበረዉ ሁኔታ አንፃር ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል " ስትል በመደነቅ ስሜት ገልጻልናለች።

እኛም ፈጣሪ ፈጽሞ እንዲምራትና ብርታቱን እንዲሰጣት ገልጸንላት ተለያየን።

የየኔነሽ አጎትና አደጋዉን ያደረሰው መኪና ባለቤት የሆኑትን አቶ ሀይሌ ሀሮንም አግኝተን ስለ አደጋዉ፣ ስለ መኪናዉ ሁኔታና ስለ ሹፌሩ ጥያቄ አቅርበንላቸው ነበር።

አቶ ሀይሌ ፥ " መኪናዉ አዲስ ነበር። ሹፌሩ ደግሞ የገዛ ወንድሜ ሲሆን ሙሽራዉም የወንድሜ ልጅ ነዉ። መኪናዉ በአባቢዉ ልምድ ከቡና ሳይት ሰራተኞችን የማመላለስ ስራ ይሰራ ስለነበርና አብዛኞቹ የቤተሰቦቻችን አባላት የቡና ስራ ስለሚሰሩ በዕለቱ ሰርገኞችን ጭኖ ወደ ወራንቻ እየሄደ ነበር አደጋዉ የተከሰተዉ " ሲሉ ነግረውናል።

አክለውም ፤ " ከቤተሰቦቻችን ብቻ ከ30 በላይ ሰዎች በአደጋዉ የሞቱ ሲሆን ከዛ ዉስጥ ግማሽ ያህሉ የወንድማማች ልጆች ናቸዉ. . . የቀን ክፉ አንገት አስደፋን ከፍተኛ የልብ ስብራት ነዉ ያጋጠመን ጌታ ብርታቱን ይስጠን " ሲሉ በሀዘን ውስጥ ሆነው አውርተውናል።

በአደጋው ምክንያት ሕይወታቸው ያጡ 71 ሥርዓተ ተቀብራቸዉ የተፈፀመ ሲሆን የሟቾችን ቤተሰብ ለማገዝ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ እየተሰባሰበ እንደሚገኝም ተረድተናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/93332
Create:
Last Update:

በተአምር የተፈረች ነፍስ !

" ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል" - ከቦናዉ የመኪና አደጋ የተረፈችው የኔነሽ ለገሠ


በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ከቀጠፈዉ የመኪና አደጋ የተረፉት 4 ሰዎች ብቻ ናቸው።

ከእነዚህ ዉስጥ ሁለቱ ገና መኪናዉ ወደ ገደል ሳይገባ ዘለዉ በመውረዳቸው መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ሁለት ሴቶች ደግሞ ተሽከርካሪዉ ወንዝ ዉስጥ ከገባ በኋላ በከፍተኛ ጉዳት በሕይወት ተርፈዉ ከቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለተሻለ ህክምና ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸዉን የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን መረጃ ያሳያል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ከዚህ አስከፊ አደጋ የተረፉትን ሁለት ሴቶች በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለመጠየቅ ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አቅንቷል።

ከአደጋው የተረፉት ሁለቱ ሴቶች ስማቸው የነኔሽ ለገሠ እና ከበቡሽ ሃይሌ ይባላሉ።

ከበቡሽ ኃይሌ በአደጋዉ ምክንያት ቀዶ ህክምና ተደርጎላት በመተንፈሻ ማሽን እርዳታ ዉስጥ ትገኛለች።

የኔነሽ ገለሠ ደግሞ በድንጋጤና ከፍተኛ ሕመም ዉስጥ ብትሆንም ማዉራት እና የተፈጠረውን አደጋ በመጠኑም ቢሆን ማስታወስና ከአስታማሚዎቿ ጋርም መግባባት ትችላለች።

ከአደጋው ስለተረፉት ሁለት ሴቶች በምን አይነት የጤንነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ማብራሪያ ከሆስፒታሉ የጠየቅን ቢሆንም ሆስፒታሉ ከአደጋው ጋር በተያያዘ " ከፖሊስ በስተቀር መረጃ ለመስጠት እንቸገራለን " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

በወቅቱ የኔነሽ ለገሰን ሲያስታምሙ ያገኘናቸው አቶ ደበበን አሁን ስላለችበት የጤና ሁኔታ ጠይቀናቸዋል።

አቶ ደበበ እንደነገሩን የኔነሽ ስለ አደጋዉ ዝርዝር ጉዳዩ እንዳልተነገራትና በዚህ ዘግናኝ አደጋ ምክንያት አንድ እህቷን እና ሁለት ወንድሞቿን ማጣቷን ነግረውናል።

በሆስፒታሉ በተገኘን ጊዜም የኔነሽ ነቃ ብላ እያወራች ነበር።

አማርኛ ቋንቋን በሚገባ መናገር ባትችልም በሲዳምኛ ቋንቋ ስለ አደጋው ስታስረዳ ማዳመጥ ችለናል።

" አደጋዉ የተከሰተዉ የአጎቴ ልጅ ሚስት ሊያገባ ስለነበር ቤተ-ዘመድ ተሰባስቦ ሙሽራዋን ለመዉሰድ ወደ ወራንቻ ቀበሌ እየሄድን በነበርንበት ወቅት ነዉ" ብላለች።

" እኔ መሃል ነበርኩ፤ ሁላችን በደስታ በዝማሬ ላይ ነበርን ወደ ዋናዉ መስመር ወጥተን ጋላና ወንዝ ስንደርስ በድንገት መኪናዉ ድልድዩን ስቶ ወደ ወንዝ መግባት ሲጀምር በጩኸት ብዛት.... " ንግግሯን መጨረሽ አልቻለችም።

ይኽን በምታወራበት ወቅት እምባ በሁለቱም ዐይኖቿ ይወርድ ነበር።

ከተወሰነ መረጋጋት በኋላ የኔነሽ ስለ አሰቃቂው አደጋ የምታስታውሰውን ማስረዳት ቀጠለች ፤ " አላዉቅም እኔ ዛሬ ነዉ ሀዋሳ መሆኔን እንኳን የተነገረኝ! ሌላዉን አላዉቅም ፤ አጎቴ አብረዉኝ ስለነበሩ አጠቃላይ ስለ ሰርገኛዉ ደጋግሜ ስጠይቀዉ 'እነሱ ቦና ናቸዉ! አንቺ ስለተጎዳሽ ነዉ እዚህ የመጣሽዉ' ይለኛል " በማለት አስታማሚዋ የነበሩት አቶ ከበደ እንደነገሩን ይኽንን መሪር ሀዘን አለመስማቷን አረጋግጣልናለች።

ይህንን በተናገረችበት ቅጽበት አጠገቧ የነበሩት ሁሉ ዝምታን መረጡ ሁሉም እንደተፈራራ ዝም ተባባለ በዚህ ጊዜ አንድ ጥያቄ ቀረበላት "ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በመትረፍሽ ምን ተሰማሽ ? " የሚል።

የኔነሽ ከነበረችበት ትካዜ በመጠኑም ነቃ ብላ " ከቦታዉ አደገኛነትና ከነበረዉ ሁኔታ አንፃር ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል " ስትል በመደነቅ ስሜት ገልጻልናለች።

እኛም ፈጣሪ ፈጽሞ እንዲምራትና ብርታቱን እንዲሰጣት ገልጸንላት ተለያየን።

የየኔነሽ አጎትና አደጋዉን ያደረሰው መኪና ባለቤት የሆኑትን አቶ ሀይሌ ሀሮንም አግኝተን ስለ አደጋዉ፣ ስለ መኪናዉ ሁኔታና ስለ ሹፌሩ ጥያቄ አቅርበንላቸው ነበር።

አቶ ሀይሌ ፥ " መኪናዉ አዲስ ነበር። ሹፌሩ ደግሞ የገዛ ወንድሜ ሲሆን ሙሽራዉም የወንድሜ ልጅ ነዉ። መኪናዉ በአባቢዉ ልምድ ከቡና ሳይት ሰራተኞችን የማመላለስ ስራ ይሰራ ስለነበርና አብዛኞቹ የቤተሰቦቻችን አባላት የቡና ስራ ስለሚሰሩ በዕለቱ ሰርገኞችን ጭኖ ወደ ወራንቻ እየሄደ ነበር አደጋዉ የተከሰተዉ " ሲሉ ነግረውናል።

አክለውም ፤ " ከቤተሰቦቻችን ብቻ ከ30 በላይ ሰዎች በአደጋዉ የሞቱ ሲሆን ከዛ ዉስጥ ግማሽ ያህሉ የወንድማማች ልጆች ናቸዉ. . . የቀን ክፉ አንገት አስደፋን ከፍተኛ የልብ ስብራት ነዉ ያጋጠመን ጌታ ብርታቱን ይስጠን " ሲሉ በሀዘን ውስጥ ሆነው አውርተውናል።

በአደጋው ምክንያት ሕይወታቸው ያጡ 71 ሥርዓተ ተቀብራቸዉ የተፈፀመ ሲሆን የሟቾችን ቤተሰብ ለማገዝ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ እየተሰባሰበ እንደሚገኝም ተረድተናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93332

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram Gives Up On Crypto Blockchain Project

Durov said on his Telegram channel today that the two and a half year blockchain and crypto project has been put to sleep. Ironically, after leaving Russia because the government wanted his encryption keys to his social media firm, Durov’s cryptocurrency idea lost steam because of a U.S. court. “The technology we created allowed for an open, free, decentralized exchange of value and ideas. TON had the potential to revolutionize how people store and transfer funds and information,” he wrote on his channel. “Unfortunately, a U.S. court stopped TON from happening.”

Importantly, that investor viewpoint is not new. It cycles in when conditions are right (and vice versa). It also brings the ineffective warnings of an overpriced market with it.Looking toward a good 2022 stock market, there is no apparent reason to expect these issues to change.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA