Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93180-93181-93182-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93182 -
Telegram Group & Telegram Channel
🚨 #ትኩረት

ዝም አትበሉ !!

በሴቶች ፣ በተለይም ምንም በማያውቁ ፤ ክፉ ደጉን እንኳን በማይለዩ ትንንሽ ህጻናት ላይ የሚፈጸመው የግብረ ስጋ መድፍረት ተግባር እጅግ አሳሳቢ እጅግም እየከፋ እየሄደ ነው።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፥ መቼም ሴት ልጆቻችን ፣ እህቶቻችን ላይ ስለሚፈጸም የአስገድዶ መድፈር / የግብረ ስጋ ድፍረትናከዛ ጋር ተያይዞ ስለሚሰጡ ፍርዶች ብዙ ጊዜ መልዕክት መለዋወጣችን ይታወሳል።

ብዙዎችሁ በምትሰሙት ፍርድ እንደምታዝኑም ህጉ ሊስተካከል እንደሚገባ ስትገልጹ ኖራችኋል።

አንዳንድ ጊዜ " እንደው የሚሰጠው ፍርድ ለጆሮ የሚቀፍ ፣ ሰው ለማስተማርና ለመቅጣት ሳይሆን ወንጀለኞችንና ግፈኞችን ለማበረታታ " እንደሚመስል በመግለጽ መሰል መረጃዎች ለብዙሃን እንዳይሰራጩ የጠየቃችሁ ሁላ አላችሁ።

በተለይ በተለይ ሴት ህጻናትን የሚደፍሩ ሰዎች ምንም በማያጠያይቅ ሁኔታ ' የሞት ቅጣት ' እንዲጣልባቸውም የሚገልጽ ሀሳብ ስትፅፉ ነበር።

ከሰሞኑን ደግሞ የተሰሙት ከህጻናት የግብረ ስጋት ድፍረት / መድፈር ጋር የተያያዙ ፍርዶች በርካታ የቲክቫህ አባላትን አስቆጥቷል፤ አሳዝኗል።

ለመረጃ ይሆናችሁ ዘንድ ...

1. ተከሳሽ ሙሉነህ ኡጋሞ የ37 ዓመት ጎልማሳ ሲሆን የባለቤቱን እህት የሆነችውን የ12 ዓመት ህጻን ከ3 ዓመት በላይ በቆየ ጊዜ ውስጥ  " ለማንም ሰው ከተናገርሽ እገልሻለሁ ! " በማለት በማስፈራራት በተደጋጋሚ አስገድዶ የግብረ ስጋት ድፍረት እንደፈጸመ የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳ የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ ገልጿል።

ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመው ባለቤቱ በወሊድ ምክንያት ታማ ለ2 ወር ሪፌራል ሆስፒታል ከተኛችበት ከቀን 11/04/2013 ዓ.ም. ወንጀሉ እስከታወቀበት 27/05/2016 ዓ.ም. ድረስ መሆኑ ነው የተገለጸው።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ14_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

2. የገዛ የአብራኩን ክፋይ የ9 ዓመት ልጁን የደፈረ ወላጅ አባት 17 ዓመት እስር ተፈርዶበታል።

ተከሳሽ አዶኒያስ አቡታ 40 ዓመቱ ሲሆን የ9 ዓመት ህጻን ልጁን በቀን 07/07/2016 ዓ.ም.ከምሽቱ 3፡30 አካባቢ ከቤተሰቦቹ ጋር ተከራይቶ በሚኖርበት ቤት ውስጥ መድፈሩን የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

ተከሳሹ ድርጊቱን የተበዳይ እናት ቤተሰቧን ለማስተዳደር በከፈተችው የቁርሳ ቁርስ ቤት ውስጥ ለማደር በሄደችበት ዕለት የፈጸመ ሲሆን ተጎጂ ህጻን ተኝታ ካለችበት ቀስቅሶ አስገድዶ መድፈሩ ነው የተጠቀሰው።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ17_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

3. የ31 ዓመቱ ከሳሽ ልደቱ አስፋ የ7 ዓመት ህጻን ከቀን 01/01/2016 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ አመት ያህል የተለያ ማባበያዎችን በመስጠት የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ሲፈጽም መቆየቱን የአቃቤ ህግ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው በህጻናት ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ18_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

4. የ5 ዓመት ህፃን ልጅ የደፈሩ 2 ግለሰቦች የ19 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል።

በወናጎ ከተማ ቱቱፈላ ቀበሌ áŠŚá‹śáˆ‹ ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ የ5 ዓመቷ ህፃን ከቀኑ 8:00 ሰዓት ዳቦ ለመግዛት በሄደችበት የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ተፈጸሞባታል።

ወንጀሉን የፈጸሙት አቶ ኤልያስ ኤቶ እና አቶ ታምሩ ንጋቱ የተባሉ የዳቦ መጋገሪያ ቤቱ ሰራተኞች ናቸው።

በግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞቹ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በወናጎ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለ ችሎት ሁለቱም ተከሳሾች እያንዳንዳቸው #በ19_ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወስኗል።

5. የ3 ዓመት ከ6 ወር ህጻን ላይ የመድፈር ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።

ወጣት ኤርምያስ ፀጋዬ 3 ዓመት ከ 6 ወር በሆነችው ተበዳይ ህፃን ከምትጫወትበት ቦታ ወደ ኤት ኤል ትምህርት ቤት ይዞ በመሄድ የመድፈር ሙከራ ማድረጉን በምስክር ያረጋገጠው የወናጎ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግለሰቡን #በ10
_ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ተጨማሪ ፦ የ28 ዓመት እድሜ ያለው ክብሮም ኣብርሃ የተባለ በትግራይ እንዳስላሰ ከተማ የሚኖር ወጣት የ11 እና 12 ዕድሜ ህፃናትን እንዲቀርቡትና እንዲላመዱት በማድረግ በጨርቅ እና በማጣበቂያ ማስቲሽ እንዳይጮሁ አፍኖ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል መፈጸሙ በመረጋገጡ #የ16_ዓመት ጽኑ እስራት ተፈርዶበታል።

ውድ የቲክቫህ አባላት ሆይ ፥ እነዚህ ያጋራናችሁ ከሰሞኑን የተላለፉ የፍርድ ውሳኔዎች ናቸው።

ድርጊቶቹ እጅግ አሰቃቂና ለጆሮም የሚከብዱ አስደንጋጭ ናቸው።

በህጻናት ላይ የሚፈጸሙ የጭካኔ ተግባራት በየጊዜው ይሰማሉ።

እኛ አሁን እየሰማን ያለነው ወደ ፍ/ቤትና ሚዲያ እየቀረቡ ያሉትን ነው በየመንደሩ በየአካባቢው ምን ያህል ልጆቻችን ጥቃት እየደረሰባቸው ይሆን ?

የፍርድ ውሳኔዎች አስተማሪ ናቸው ?

ልጆቻችንን ከዚህ የከፋ እና አስፈሪ ጊዜ ለመጠበቅ ምን መደረግ አለበት ?

መፍትሄው ምን ይሆን ?

በዚህ ጉዳይ ላይ የህግ ባለሙያ አስተያየት በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል። እናተም የሚሰማችሁን በ @tikvahethiopiaBot ላይ ፃፉ።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/93182
Create:
Last Update:

🚨 #ትኩረት

ዝም አትበሉ !!

በሴቶች ፣ በተለይም ምንም በማያውቁ ፤ ክፉ ደጉን እንኳን በማይለዩ ትንንሽ ህጻናት ላይ የሚፈጸመው የግብረ ስጋ መድፍረት ተግባር እጅግ አሳሳቢ እጅግም እየከፋ እየሄደ ነው።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፥ መቼም ሴት ልጆቻችን ፣ እህቶቻችን ላይ ስለሚፈጸም የአስገድዶ መድፈር / የግብረ ስጋ ድፍረትናከዛ ጋር ተያይዞ ስለሚሰጡ ፍርዶች ብዙ ጊዜ መልዕክት መለዋወጣችን ይታወሳል።

ብዙዎችሁ በምትሰሙት ፍርድ እንደምታዝኑም ህጉ ሊስተካከል እንደሚገባ ስትገልጹ ኖራችኋል።

አንዳንድ ጊዜ " እንደው የሚሰጠው ፍርድ ለጆሮ የሚቀፍ ፣ ሰው ለማስተማርና ለመቅጣት ሳይሆን ወንጀለኞችንና ግፈኞችን ለማበረታታ " እንደሚመስል በመግለጽ መሰል መረጃዎች ለብዙሃን እንዳይሰራጩ የጠየቃችሁ ሁላ አላችሁ።

በተለይ በተለይ ሴት ህጻናትን የሚደፍሩ ሰዎች ምንም በማያጠያይቅ ሁኔታ ' የሞት ቅጣት ' እንዲጣልባቸውም የሚገልጽ ሀሳብ ስትፅፉ ነበር።

ከሰሞኑን ደግሞ የተሰሙት ከህጻናት የግብረ ስጋት ድፍረት / መድፈር ጋር የተያያዙ ፍርዶች በርካታ የቲክቫህ አባላትን አስቆጥቷል፤ አሳዝኗል።

ለመረጃ ይሆናችሁ ዘንድ ...

1. ተከሳሽ ሙሉነህ ኡጋሞ የ37 ዓመት ጎልማሳ ሲሆን የባለቤቱን እህት የሆነችውን የ12 ዓመት ህጻን ከ3 ዓመት በላይ በቆየ ጊዜ ውስጥ  " ለማንም ሰው ከተናገርሽ እገልሻለሁ ! " በማለት በማስፈራራት በተደጋጋሚ አስገድዶ የግብረ ስጋት ድፍረት እንደፈጸመ የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳ የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ ገልጿል።

ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመው ባለቤቱ በወሊድ ምክንያት ታማ ለ2 ወር ሪፌራል ሆስፒታል ከተኛችበት ከቀን 11/04/2013 ዓ.ም. ወንጀሉ እስከታወቀበት 27/05/2016 ዓ.ም. ድረስ መሆኑ ነው የተገለጸው።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ14_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

2. የገዛ የአብራኩን ክፋይ የ9 ዓመት ልጁን የደፈረ ወላጅ አባት 17 ዓመት እስር ተፈርዶበታል።

ተከሳሽ አዶኒያስ አቡታ 40 ዓመቱ ሲሆን የ9 ዓመት ህጻን ልጁን በቀን 07/07/2016 ዓ.ም.ከምሽቱ 3፡30 አካባቢ ከቤተሰቦቹ ጋር ተከራይቶ በሚኖርበት ቤት ውስጥ መድፈሩን የዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

ተከሳሹ ድርጊቱን የተበዳይ እናት ቤተሰቧን ለማስተዳደር በከፈተችው የቁርሳ ቁርስ ቤት ውስጥ ለማደር በሄደችበት ዕለት የፈጸመ ሲሆን ተጎጂ ህጻን ተኝታ ካለችበት ቀስቅሶ አስገድዶ መድፈሩ ነው የተጠቀሰው።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ17_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

3. የ31 ዓመቱ ከሳሽ ልደቱ አስፋ የ7 ዓመት ህጻን ከቀን 01/01/2016 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ አመት ያህል የተለያ ማባበያዎችን በመስጠት የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ሲፈጽም መቆየቱን የአቃቤ ህግ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

የቀረበውን ክስ ተቀብሎ ሲያከራክር የቆየው የሀዋሳ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም. በዋለው በህጻናት ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት #በ18_ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

4. የ5 ዓመት ህፃን ልጅ የደፈሩ 2 ግለሰቦች የ19 ዓመት እስር ተፈርዶባቸዋል።

በወናጎ ከተማ ቱቱፈላ ቀበሌ áŠŚá‹śáˆ‹ ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ የ5 ዓመቷ ህፃን ከቀኑ 8:00 ሰዓት ዳቦ ለመግዛት በሄደችበት የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ተፈጸሞባታል።

ወንጀሉን የፈጸሙት አቶ ኤልያስ ኤቶ እና አቶ ታምሩ ንጋቱ የተባሉ የዳቦ መጋገሪያ ቤቱ ሰራተኞች ናቸው።

በግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞቹ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በወናጎ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለ ችሎት ሁለቱም ተከሳሾች እያንዳንዳቸው #በ19_ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወስኗል።

5. የ3 ዓመት ከ6 ወር ህጻን ላይ የመድፈር ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።

ወጣት ኤርምያስ ፀጋዬ 3 ዓመት ከ 6 ወር በሆነችው ተበዳይ ህፃን ከምትጫወትበት ቦታ ወደ ኤት ኤል ትምህርት ቤት ይዞ በመሄድ የመድፈር ሙከራ ማድረጉን በምስክር ያረጋገጠው የወናጎ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግለሰቡን #በ10
_ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ተጨማሪ ፦ የ28 ዓመት እድሜ ያለው ክብሮም ኣብርሃ የተባለ በትግራይ እንዳስላሰ ከተማ የሚኖር ወጣት የ11 እና 12 ዕድሜ ህፃናትን እንዲቀርቡትና እንዲላመዱት በማድረግ በጨርቅ እና በማጣበቂያ ማስቲሽ እንዳይጮሁ አፍኖ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል መፈጸሙ በመረጋገጡ #የ16_ዓመት ጽኑ እስራት ተፈርዶበታል።

ውድ የቲክቫህ አባላት ሆይ ፥ እነዚህ ያጋራናችሁ ከሰሞኑን የተላለፉ የፍርድ ውሳኔዎች ናቸው።

ድርጊቶቹ እጅግ አሰቃቂና ለጆሮም የሚከብዱ አስደንጋጭ ናቸው።

በህጻናት ላይ የሚፈጸሙ የጭካኔ ተግባራት በየጊዜው ይሰማሉ።

እኛ አሁን እየሰማን ያለነው ወደ ፍ/ቤትና ሚዲያ እየቀረቡ ያሉትን ነው በየመንደሩ በየአካባቢው ምን ያህል ልጆቻችን ጥቃት እየደረሰባቸው ይሆን ?

የፍርድ ውሳኔዎች አስተማሪ ናቸው ?

ልጆቻችንን ከዚህ የከፋ እና አስፈሪ ጊዜ ለመጠበቅ ምን መደረግ አለበት ?

መፍትሄው ምን ይሆን ?

በዚህ ጉዳይ ላይ የህግ ባለሙያ አስተያየት በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል። እናተም የሚሰማችሁን በ @tikvahethiopiaBot ላይ ፃፉ።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93182

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The SSE was the first modern stock exchange to open in China, with trading commencing in 1990. It has now grown to become the largest stock exchange in Asia and the third-largest in the world by market capitalization, which stood at RMB 50.6 trillion (US$7.8 trillion) as of September 2021. Stocks (both A-shares and B-shares), bonds, funds, and derivatives are traded on the exchange. The SEE has two trading boards, the Main Board and the Science and Technology Innovation Board, the latter more commonly known as the STAR Market. The Main Board mainly hosts large, well-established Chinese companies and lists both A-shares and B-shares.

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA