#AddisAbaba
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/92515
Create:
Last Update:
Last Update:
#AddisAbaba
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA



Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/92515