Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-92008-92009-92010-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/92010 -
Telegram Group & Telegram Channel
#ጋምቤላ

አዲስ አመራር ከመጣ በኃላ በጋምቤላ መሻሻል ታይቷል ?

በጋምቤላ ክልል ካለፈው ነሐሴ 2016 ዓ/ም ወዲህ የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ በክልሉ የነበረው የሠላም ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን አዲሱ አስተዳደር፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በጋምቤላ ክልል በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜዎች ግጭቶች እየተከሰቱ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል።

ከሰብዓዊ ጉዳቱ ባሻገር በክልሉ ነዋሪዎች መካክል የነበሩ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ቦታዎች እስከመገደብ ደርሰውም ነበር።

የክልሉ ልማትና ሰላምም በእጅጉ ተጎደቶ ነበር።

በተለይ ቀደም ባሉት ጊዜዎች የአኙዋክ ተውላጆች ወደ ኑዌር ሰፈር አይሄዱም፣ ኑዌሮችም በተመሳሳይ ወደ አኙዋክ ሰፈር ይሻገሩ አልነበረም።

አሁን ላይ ግን ሁኔታዎች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን የጋምቤላ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ጋትሏክ ሮን ምን አሉ ?

- ችግሮችን ለማስተካክልና በክልሉ ሠላም ለማስፈንና ህዝቡን ወደልማት ለማምጣት በክልሉ ከነሐሴ 2016 ዓ/ም መጀመሪያ ሳምንት ላይ የአመራር ለውጥ በመደረጉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሠላም ሰፍኗል።

- በክልሉ በነበረው የሠላም እጦት ምክንያት የጋምቤላ ከተማ የአኙዋክና የኑዌር በሚል ተከፍሎ አኙዋኮች ወደ ኑዌር ሰፈር፣ ኑዌሮችም ወደ አኙዋክ መንደር ለመሻገር ችግሮች ነበሩ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ አዲሱ አመራር ወደ ሥራ ከገባና ህዝባዊ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሁሉም በሠላም በሁሉም ሥፍራ ይንቀሳቀሳል።

🔵 ማሉት ዴቪድ የተባሉ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ሀሳብ ይጋሩታል፣ አሁን አንዱ ወደ ሌላው ያለስጋት እንደሚንቀሳቀስ ነው ያረጋገጡት። ከተማውም ሠላም እንደሆን አመልክተዋል።

- አዳዲስ ሹመቶችና ምደባዎች ተሰጥተዋል። ይህም የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን መሠረት ያደረገ ነው።

- ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ የታመነባቸው ቀደም ሲል ስልጣን ላይ የነበሩና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸው በርከት ያሉ አመራሮችም በአዲሱ ሹመትና ምደባ እንደገና  ተካተዋል።

- " ሠላም ወርዶ ህዝቡ በልማት መካስ አለበት " በሚል እሳቤ እውቀት፣ ልምድና የተሻል አመለካክትና እይታ ያላችው ሠዎች ወደ አመራሩ ተካተዋል።

- በኮታ መታሰር ቀርቷል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ወንጀል ያልሰሩ ሰዎች በኮታ ጭምር ይታሰሩ ነበር። አሁን ግን በወንጀል የተጠረጠሩትን ብቻ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቷል።

- በፊት አንድ ኑዌር ቢያጠፋና ቢታሰር ሌላ አኙዋክ አብሮ እንዲታሰር ይደረግ ነበር፣ ሌላ አኙዋክ አጥፍቶ ቢታሰር  የኑዌር ተወላጅ ተደርቦ እንዲታሰር ይደረግ ነበር ፤ አሁን ግን ጠፋተኛው ከየትኛውም ወገን ይሁን ጠፋተኛ ከሆን ተጠርጣሪው ብቻ ተለይቶ ተጠያቂ ይሆናል። የኮታ እስር ቀርቷል።

" ከአዲሱ አመራር ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ " - ጋብዴን

የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጋብዴን) ሊቀመንበር አቶ ኡባንግ ኡሞድ ቀደም ሲል የነበረው አመራር ህዝቡን መምራት እንዳልቻለና ለውጥ እንዲመጣ ሲታግሉ እንደንበር ገልጠዋል።

ችግሩ የአመራሩ ሆኖ ሳለ ህዝቡን በከፍተኛ የሠላም እጦት ውስጥ ከትቶት ነበር ነው ያሉት።

በክልሉ የነበረውን ችግር እስከ የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት በማድረስ የነበረው የሠላም እጦት እንዲታወቅ መደረጉንና ለውጥ እንዲደረግ በግልም በጋራም ትግል ሲደረግ እንደነበር አስረድተዋል። 

አዲሶቹ አመራሮች በሕዝቡ ተቀባይነት ማግኘታቸውንና ፓርቲያቸውም በአዲሱ አመራር ደስተኛ መሆኑን አቶ ኡባንግ ተናግረዋል።

ከአዲሱ አመራር ጋርም በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑም ነው የገለጡት። 

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ነሐሴ 9/2016 ዓ ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡመድን የመጀመሪያዋ የክልል ሴት ርዕሰ መስተዳድር፣ ዶ/ር ጋትሏክ ሮንን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/92010
Create:
Last Update:

#ጋምቤላ

አዲስ አመራር ከመጣ በኃላ በጋምቤላ መሻሻል ታይቷል ?

በጋምቤላ ክልል ካለፈው ነሐሴ 2016 ዓ/ም ወዲህ የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ በክልሉ የነበረው የሠላም ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን አዲሱ አስተዳደር፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በጋምቤላ ክልል በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜዎች ግጭቶች እየተከሰቱ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል።

ከሰብዓዊ ጉዳቱ ባሻገር በክልሉ ነዋሪዎች መካክል የነበሩ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ቦታዎች እስከመገደብ ደርሰውም ነበር።

የክልሉ ልማትና ሰላምም በእጅጉ ተጎደቶ ነበር።

በተለይ ቀደም ባሉት ጊዜዎች የአኙዋክ ተውላጆች ወደ ኑዌር ሰፈር አይሄዱም፣ ኑዌሮችም በተመሳሳይ ወደ አኙዋክ ሰፈር ይሻገሩ አልነበረም።

አሁን ላይ ግን ሁኔታዎች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን የጋምቤላ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ጋትሏክ ሮን ምን አሉ ?

- ችግሮችን ለማስተካክልና በክልሉ ሠላም ለማስፈንና ህዝቡን ወደልማት ለማምጣት በክልሉ ከነሐሴ 2016 ዓ/ም መጀመሪያ ሳምንት ላይ የአመራር ለውጥ በመደረጉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሠላም ሰፍኗል።

- በክልሉ በነበረው የሠላም እጦት ምክንያት የጋምቤላ ከተማ የአኙዋክና የኑዌር በሚል ተከፍሎ አኙዋኮች ወደ ኑዌር ሰፈር፣ ኑዌሮችም ወደ አኙዋክ መንደር ለመሻገር ችግሮች ነበሩ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ አዲሱ አመራር ወደ ሥራ ከገባና ህዝባዊ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሁሉም በሠላም በሁሉም ሥፍራ ይንቀሳቀሳል።

🔵 ማሉት ዴቪድ የተባሉ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ሀሳብ ይጋሩታል፣ አሁን አንዱ ወደ ሌላው ያለስጋት እንደሚንቀሳቀስ ነው ያረጋገጡት። ከተማውም ሠላም እንደሆን አመልክተዋል።

- አዳዲስ ሹመቶችና ምደባዎች ተሰጥተዋል። ይህም የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን መሠረት ያደረገ ነው።

- ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ የታመነባቸው ቀደም ሲል ስልጣን ላይ የነበሩና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸው በርከት ያሉ አመራሮችም በአዲሱ ሹመትና ምደባ እንደገና  ተካተዋል።

- " ሠላም ወርዶ ህዝቡ በልማት መካስ አለበት " በሚል እሳቤ እውቀት፣ ልምድና የተሻል አመለካክትና እይታ ያላችው ሠዎች ወደ አመራሩ ተካተዋል።

- በኮታ መታሰር ቀርቷል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ወንጀል ያልሰሩ ሰዎች በኮታ ጭምር ይታሰሩ ነበር። አሁን ግን በወንጀል የተጠረጠሩትን ብቻ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቷል።

- በፊት አንድ ኑዌር ቢያጠፋና ቢታሰር ሌላ አኙዋክ አብሮ እንዲታሰር ይደረግ ነበር፣ ሌላ አኙዋክ አጥፍቶ ቢታሰር  የኑዌር ተወላጅ ተደርቦ እንዲታሰር ይደረግ ነበር ፤ አሁን ግን ጠፋተኛው ከየትኛውም ወገን ይሁን ጠፋተኛ ከሆን ተጠርጣሪው ብቻ ተለይቶ ተጠያቂ ይሆናል። የኮታ እስር ቀርቷል።

" ከአዲሱ አመራር ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ " - ጋብዴን

የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጋብዴን) ሊቀመንበር አቶ ኡባንግ ኡሞድ ቀደም ሲል የነበረው አመራር ህዝቡን መምራት እንዳልቻለና ለውጥ እንዲመጣ ሲታግሉ እንደንበር ገልጠዋል።

ችግሩ የአመራሩ ሆኖ ሳለ ህዝቡን በከፍተኛ የሠላም እጦት ውስጥ ከትቶት ነበር ነው ያሉት።

በክልሉ የነበረውን ችግር እስከ የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት በማድረስ የነበረው የሠላም እጦት እንዲታወቅ መደረጉንና ለውጥ እንዲደረግ በግልም በጋራም ትግል ሲደረግ እንደነበር አስረድተዋል። 

አዲሶቹ አመራሮች በሕዝቡ ተቀባይነት ማግኘታቸውንና ፓርቲያቸውም በአዲሱ አመራር ደስተኛ መሆኑን አቶ ኡባንግ ተናግረዋል።

ከአዲሱ አመራር ጋርም በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑም ነው የገለጡት። 

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ነሐሴ 9/2016 ዓ ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡመድን የመጀመሪያዋ የክልል ሴት ርዕሰ መስተዳድር፣ ዶ/ር ጋትሏክ ሮንን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/92010

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram auto-delete message, expiring invites, and more

elegram is updating its messaging app with options for auto-deleting messages, expiring invite links, and new unlimited groups, the company shared in a blog post. Much like Signal, Telegram received a burst of new users in the confusion over WhatsApp’s privacy policy and now the company is adopting features that were already part of its competitors’ apps, features which offer more security and privacy. Auto-deleting messages were already possible in Telegram’s encrypted Secret Chats, but this new update for iOS and Android adds the option to make messages disappear in any kind of chat. Auto-delete can be enabled inside of chats, and set to delete either 24 hours or seven days after messages are sent. Auto-delete won’t remove every message though; if a message was sent before the feature was turned on, it’ll stick around. Telegram’s competitors have had similar features: WhatsApp introduced a feature in 2020 and Signal has had disappearing messages since at least 2016.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA