Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-92002-92003-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/92002 -
Telegram Group & Telegram Channel
" የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል " - የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል

የአላቂ እቃዎች እጥረት የህፃናት ታካሚዎችን ወረፋ እየጨመረው መሆኑን፣ አሁንም ድረስ በአቬሬጅ አራት ዓመት ለሚሆን ጊዜ ወረፋ እየጠበቁ ያሉ ወደ 8,000 የሚጠጉ ህፃናት እንዳሉ የኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል ለቲክህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የማዕከሉ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባልደረባ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ በሰጡን ቃል፣ " የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል" ብለዋል።

በማዕከሉ አጣዳፊ ትኩረት የሚሻው ፈታኝ ጉዳይ ምንድን ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።

ዶ/ር ዳዊት ፥ " እያጋጠመን ያለው አንዱና ትልቁ ፈተና የአላቂ እቃዎች ነው። የምንሰጣቸው አገልግሎቶች በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አገልግሎት ላይ ለሚውሉ እቃዎች በተለያዩ ምክንያቶች እጥረት አለ " ብለዋል።

" የአላቂ እቃዎች እንደልብ አለመገኘት የታካሚ የወረፋ ጊዜን እየጨመረው ይገኛል። አሁንም ወደ 8,000 የሚጠጉ ህፃናት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

" አቬሬጅ የወረፋ ጊዜ አራት ዓመት እየደረሰ ነው ። በዋናነኝነት ከምንጠቀማቸው እቃዎች በተጨማሪ በዬቀኑ አክቲቪቲው ላይ የሚውሉ ለኦፕሬሽንና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ መድኃኒቶች/የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል " ብለዋል።

በአቬሬጅ ለአራት ዓመት ወረፋ እየጠበቁ ያሉ ህፃናት ቢያንስ በምን ያክል ጊዜ ነበር ህክምና ማግኘት የነበረባቸው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ " በዓመት እስከ 500 ታካሚዎችን እናስተናግዳለን። በሙሉ አቅማችን ግን ብንሰራ እስከ 1500 ህፃናትን መድረስ እንችላለን " ሲሉ መልሰዋል።

" ችግሩ ግን በዓመት 1,300 ያህል አዳዲስ ታካሚዎች ይኖራሉ። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት ከ20 ሺሕ በላይ ህፃናት በተፈጥሮ ከሚመጣ የልብ ችግር ጋር ይወለዳሉ ይባላል በዓመት። ስለዚህ ይሄ ችግር ውጪ አገር ቶሎ ነው መፍትሄ የሚሰጠው አገልግሎቱ አቬሌብል ስለሆነ። ወዲያው ቢሆን ይመረጣል "  ነው ያሉት።

እጥረት እየተስተዋለባቸው ያሉ የእቃ አይነቶች ምንድን ናቸው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ ፦

" ለልብ ህክምና የሚያስፈልጉ መድኃኒቶች አሉ። እንደ የደም ማቅጠኛ አይነት መድኃኒቶች ናቸው። ሁለት አይነት አገልግሎቶችን ነው የምንሰጠው በኛ ማዕከል። 

አንደኛው ደረት ተከፍቶ የሚሰራው ቀዶ ህክምና ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በደም ስር ውስጥ ተኪዶ የልብ ጥገናው የሚካሄድበት አገልግሎቶች ናቸው። እያንዳንዳቸውም የሚጠቀሟቸው ማተሪያሎች አሉ።

በቀዶ ህክምናው ኦክስጂኔተር የሚባል አለ። የልብና የሳንባውን ሥራ ተክቶ የሚሰራው ማሽን ላይ የሚገጠም ነው። እሱ ማተሪያል ለአንድ ጊዜ ነው አገልግሎት ላይ የሚውለው። ለአንድ ታካሚ ለአንዴ ነው የሚሆነው።

ካትላብ ላይ ደግሞ በደም ስር ውስጥ ዋየሮች የተለያዬ የዋጋ ሬንጅ አላቸው። እነርሱን እኛ ጋ አጥበን እስከ 4፣ 5 ጊዜ ደጋግመን እንጠቀማቸዋለን።

ስለዚህ በዋነኝነት እነዚህ ማተሪያሎች፣ ከዚያ ደግሞ የተለያዩ ኬሚካሎች ሁሉ አላቂ ከምንላቸው እቃዎች ውስጥ ይካተታሉ
" ሲሉ መልሰዋል።

የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል ላለፉት 35 ዓመታት አገልግሎቱን በመስጠት ላይ ይገኛል።

በመጀመሪያዎቹ 20 ዓመታት ህክምና ሲሰጥ የነበረው ወደ ውጪ በመላክ ነበር። በዚህም ወደ 2,600 ገደማ ህፃናት ውጪ ሂደው እንደታከሙ፣ ላለፉት 15 ዓመታት ደግሞ አሁን ባለው ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ ነው።

በአጠቃይ እስካሁን 9,000 ህፃናት የልብ ቀዶ ጥገና እንደተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/92002
Create:
Last Update:

" የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል " - የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል

የአላቂ እቃዎች እጥረት የህፃናት ታካሚዎችን ወረፋ እየጨመረው መሆኑን፣ አሁንም ድረስ በአቬሬጅ አራት ዓመት ለሚሆን ጊዜ ወረፋ እየጠበቁ ያሉ ወደ 8,000 የሚጠጉ ህፃናት እንዳሉ የኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል ለቲክህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የማዕከሉ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባልደረባ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ በሰጡን ቃል፣ " የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል" ብለዋል።

በማዕከሉ አጣዳፊ ትኩረት የሚሻው ፈታኝ ጉዳይ ምንድን ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።

ዶ/ር ዳዊት ፥ " እያጋጠመን ያለው አንዱና ትልቁ ፈተና የአላቂ እቃዎች ነው። የምንሰጣቸው አገልግሎቶች በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አገልግሎት ላይ ለሚውሉ እቃዎች በተለያዩ ምክንያቶች እጥረት አለ " ብለዋል።

" የአላቂ እቃዎች እንደልብ አለመገኘት የታካሚ የወረፋ ጊዜን እየጨመረው ይገኛል። አሁንም ወደ 8,000 የሚጠጉ ህፃናት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።

" አቬሬጅ የወረፋ ጊዜ አራት ዓመት እየደረሰ ነው ። በዋናነኝነት ከምንጠቀማቸው እቃዎች በተጨማሪ በዬቀኑ አክቲቪቲው ላይ የሚውሉ ለኦፕሬሽንና ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ መድኃኒቶች/የአላቂ እቃዎች እጥረት በጣም ትልቅ ፈተና ሆኖብናል " ብለዋል።

በአቬሬጅ ለአራት ዓመት ወረፋ እየጠበቁ ያሉ ህፃናት ቢያንስ በምን ያክል ጊዜ ነበር ህክምና ማግኘት የነበረባቸው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ " በዓመት እስከ 500 ታካሚዎችን እናስተናግዳለን። በሙሉ አቅማችን ግን ብንሰራ እስከ 1500 ህፃናትን መድረስ እንችላለን " ሲሉ መልሰዋል።

" ችግሩ ግን በዓመት 1,300 ያህል አዳዲስ ታካሚዎች ይኖራሉ። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት ከ20 ሺሕ በላይ ህፃናት በተፈጥሮ ከሚመጣ የልብ ችግር ጋር ይወለዳሉ ይባላል በዓመት። ስለዚህ ይሄ ችግር ውጪ አገር ቶሎ ነው መፍትሄ የሚሰጠው አገልግሎቱ አቬሌብል ስለሆነ። ወዲያው ቢሆን ይመረጣል "  ነው ያሉት።

እጥረት እየተስተዋለባቸው ያሉ የእቃ አይነቶች ምንድን ናቸው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ ፦

" ለልብ ህክምና የሚያስፈልጉ መድኃኒቶች አሉ። እንደ የደም ማቅጠኛ አይነት መድኃኒቶች ናቸው። ሁለት አይነት አገልግሎቶችን ነው የምንሰጠው በኛ ማዕከል። 

አንደኛው ደረት ተከፍቶ የሚሰራው ቀዶ ህክምና ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በደም ስር ውስጥ ተኪዶ የልብ ጥገናው የሚካሄድበት አገልግሎቶች ናቸው። እያንዳንዳቸውም የሚጠቀሟቸው ማተሪያሎች አሉ።

በቀዶ ህክምናው ኦክስጂኔተር የሚባል አለ። የልብና የሳንባውን ሥራ ተክቶ የሚሰራው ማሽን ላይ የሚገጠም ነው። እሱ ማተሪያል ለአንድ ጊዜ ነው አገልግሎት ላይ የሚውለው። ለአንድ ታካሚ ለአንዴ ነው የሚሆነው።

ካትላብ ላይ ደግሞ በደም ስር ውስጥ ዋየሮች የተለያዬ የዋጋ ሬንጅ አላቸው። እነርሱን እኛ ጋ አጥበን እስከ 4፣ 5 ጊዜ ደጋግመን እንጠቀማቸዋለን።

ስለዚህ በዋነኝነት እነዚህ ማተሪያሎች፣ ከዚያ ደግሞ የተለያዩ ኬሚካሎች ሁሉ አላቂ ከምንላቸው እቃዎች ውስጥ ይካተታሉ
" ሲሉ መልሰዋል።

የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል ላለፉት 35 ዓመታት አገልግሎቱን በመስጠት ላይ ይገኛል።

በመጀመሪያዎቹ 20 ዓመታት ህክምና ሲሰጥ የነበረው ወደ ውጪ በመላክ ነበር። በዚህም ወደ 2,600 ገደማ ህፃናት ውጪ ሂደው እንደታከሙ፣ ላለፉት 15 ዓመታት ደግሞ አሁን ባለው ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ ነው።

በአጠቃይ እስካሁን 9,000 ህፃናት የልብ ቀዶ ጥገና እንደተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/92002

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Why Telegram?

Telegram has no known backdoors and, even though it is come in for criticism for using proprietary encryption methods instead of open-source ones, those have yet to be compromised. While no messaging app can guarantee a 100% impermeable defense against determined attackers, Telegram is vulnerabilities are few and either theoretical or based on spoof files fooling users into actively enabling an attack.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA