#ሞዛምቢክ
• 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ገዢ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ተቃውሞና አመጽ ቀስቅሷል።
በአፍሪካዊቷ ሀገር ሞዛምቢክ ባለፈው ወር ላይ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።
ለረጅም አመታት ስልጣን ላይ የቆየው ገዢ ፓርቲ ዕጩ ዳንኤል ቻፖ " ምርጫውን አሸነፉ " መባሉ ከፍተኛ ተቃውሞ እና አመጽ ቀስቅሶ ሰዎች ተገድለዋል።
የአደባባይ ተቃውሞዎችም እየተደረጉ ነው።
አወዛጋቢ ነው በተባለው ምርጫ አሸንፏል የተባለውን " ፍሬሊሞ " የተሰኘውን ገዢ ፓርቲ ለመቃወም ዛሬ ማፑቶ ላይ ሰልፍ የወጡ ብዙሃኑ ወጣቶችን የፀጥታ ኃይሎች የአስለቃሽ ጭስ እየተኮሱ ሲያሳድዱ ውለዋል።
ምርጫውን " አሸንፏል " የተባለው ፓርቲ 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ሲሆን የምርጫ ውጤቱ የ49 ዓመታት ስልጣኑን ለማራዘም ያስችለዋል ተብሏል።
ይሄ ገዢ ፓርቲ እ.ኤ.አ ከ1975 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል።
የፍሬሊሞ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ይፋ ከተደረገ በኃላ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ 18 ሰዎች በፖሊስ መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገልጸዋል።
ምርጫው ከፍተኛ ፉክክር የተደረገበት ነበር የተባለ ሲሆን ብዙሃኑ ወጣቶች ዋነኛውን ተቀናቃኝ የ ' ፖዴሞስ ' መሪ ቬንሢዮ ሞንዳኔ ደግፈው ድምጽ መስጥታቸው ተነግሯል።
እሳቸውም ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ገልጸው ተቃውሞዎችን አበረታተዋል።
ምርጫው መጭበርበሩን ብቻ ሳይሆን እሳቸው እንዳሸነፉ የገለጹት ሞንዳኔ ፥ የግድያ ሙከራ ጭምር ተደርጎባቸው እንዳመለጡ ገልጸዋል።
ጠበቃቸው መገደላቸውንም ጠቁመዋል።
አሁን ላይም ሀገር ውስጥ እንደማይገኙ ተነግሯል።
ዛሬ በዋና ከተማይቱ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የተቆጡ ሰልፈኞች " ስልጣን ለህዝብ " ፣ " ውድቀት ለፍሬሊሞ " እና " ፍሬሊሞ መውደቅ አለበት " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ተጠቅመው ሰልፉን በትነዋል።
አንድ እድሜያቸው 55 የሆነ የ6 ልጆች እናት " አሁን ካልተነሳን ምንም ለውጥ አይመጣም " ሲሉ ተናግረዋል።
" የፍሬሊሞ ጀርባ የሚታይበት ጊዜው አሁን ነው " ብለዋል።
ህዝባዊ ተቃውሞው ከተባባሰ በኋላ የሀገሪቱ ተሰናባች ፕሬዝዳንት ፊሊፔ ኑዩሲ ትንፍሽ አላሉም።
የመከላከያ ሚኒስትራቸው ግን ወጥተው ወታደሩን እንደሚያሰማሩ እና ስልጣን በኃይል ለማያዝ ሙከራ እንዳይደረግ አስጠንቅቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ማሰባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
• 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ገዢ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ተቃውሞና አመጽ ቀስቅሷል።
በአፍሪካዊቷ ሀገር ሞዛምቢክ ባለፈው ወር ላይ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።
ለረጅም አመታት ስልጣን ላይ የቆየው ገዢ ፓርቲ ዕጩ ዳንኤል ቻፖ " ምርጫውን አሸነፉ " መባሉ ከፍተኛ ተቃውሞ እና አመጽ ቀስቅሶ ሰዎች ተገድለዋል።
የአደባባይ ተቃውሞዎችም እየተደረጉ ነው።
አወዛጋቢ ነው በተባለው ምርጫ አሸንፏል የተባለውን " ፍሬሊሞ " የተሰኘውን ገዢ ፓርቲ ለመቃወም ዛሬ ማፑቶ ላይ ሰልፍ የወጡ ብዙሃኑ ወጣቶችን የፀጥታ ኃይሎች የአስለቃሽ ጭስ እየተኮሱ ሲያሳድዱ ውለዋል።
ምርጫውን " አሸንፏል " የተባለው ፓርቲ 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ሲሆን የምርጫ ውጤቱ የ49 ዓመታት ስልጣኑን ለማራዘም ያስችለዋል ተብሏል።
ይሄ ገዢ ፓርቲ እ.ኤ.አ ከ1975 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል።
የፍሬሊሞ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ይፋ ከተደረገ በኃላ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ 18 ሰዎች በፖሊስ መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገልጸዋል።
ምርጫው ከፍተኛ ፉክክር የተደረገበት ነበር የተባለ ሲሆን ብዙሃኑ ወጣቶች ዋነኛውን ተቀናቃኝ የ ' ፖዴሞስ ' መሪ ቬንሢዮ ሞንዳኔ ደግፈው ድምጽ መስጥታቸው ተነግሯል።
እሳቸውም ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ገልጸው ተቃውሞዎችን አበረታተዋል።
ምርጫው መጭበርበሩን ብቻ ሳይሆን እሳቸው እንዳሸነፉ የገለጹት ሞንዳኔ ፥ የግድያ ሙከራ ጭምር ተደርጎባቸው እንዳመለጡ ገልጸዋል።
ጠበቃቸው መገደላቸውንም ጠቁመዋል።
አሁን ላይም ሀገር ውስጥ እንደማይገኙ ተነግሯል።
ዛሬ በዋና ከተማይቱ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የተቆጡ ሰልፈኞች " ስልጣን ለህዝብ " ፣ " ውድቀት ለፍሬሊሞ " እና " ፍሬሊሞ መውደቅ አለበት " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ተጠቅመው ሰልፉን በትነዋል።
አንድ እድሜያቸው 55 የሆነ የ6 ልጆች እናት " አሁን ካልተነሳን ምንም ለውጥ አይመጣም " ሲሉ ተናግረዋል።
" የፍሬሊሞ ጀርባ የሚታይበት ጊዜው አሁን ነው " ብለዋል።
ህዝባዊ ተቃውሞው ከተባባሰ በኋላ የሀገሪቱ ተሰናባች ፕሬዝዳንት ፊሊፔ ኑዩሲ ትንፍሽ አላሉም።
የመከላከያ ሚኒስትራቸው ግን ወጥተው ወታደሩን እንደሚያሰማሩ እና ስልጣን በኃይል ለማያዝ ሙከራ እንዳይደረግ አስጠንቅቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ማሰባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/91991
Create:
Last Update:
Last Update:
#ሞዛምቢክ
• 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ገዢ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ተቃውሞና አመጽ ቀስቅሷል።
በአፍሪካዊቷ ሀገር ሞዛምቢክ ባለፈው ወር ላይ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።
ለረጅም አመታት ስልጣን ላይ የቆየው ገዢ ፓርቲ ዕጩ ዳንኤል ቻፖ " ምርጫውን አሸነፉ " መባሉ ከፍተኛ ተቃውሞ እና አመጽ ቀስቅሶ ሰዎች ተገድለዋል።
የአደባባይ ተቃውሞዎችም እየተደረጉ ነው።
አወዛጋቢ ነው በተባለው ምርጫ አሸንፏል የተባለውን " ፍሬሊሞ " የተሰኘውን ገዢ ፓርቲ ለመቃወም ዛሬ ማፑቶ ላይ ሰልፍ የወጡ ብዙሃኑ ወጣቶችን የፀጥታ ኃይሎች የአስለቃሽ ጭስ እየተኮሱ ሲያሳድዱ ውለዋል።
ምርጫውን " አሸንፏል " የተባለው ፓርቲ 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ሲሆን የምርጫ ውጤቱ የ49 ዓመታት ስልጣኑን ለማራዘም ያስችለዋል ተብሏል።
ይሄ ገዢ ፓርቲ እ.ኤ.አ ከ1975 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል።
የፍሬሊሞ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ይፋ ከተደረገ በኃላ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ 18 ሰዎች በፖሊስ መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገልጸዋል።
ምርጫው ከፍተኛ ፉክክር የተደረገበት ነበር የተባለ ሲሆን ብዙሃኑ ወጣቶች ዋነኛውን ተቀናቃኝ የ ' ፖዴሞስ ' መሪ ቬንሢዮ ሞንዳኔ ደግፈው ድምጽ መስጥታቸው ተነግሯል።
እሳቸውም ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ገልጸው ተቃውሞዎችን አበረታተዋል።
ምርጫው መጭበርበሩን ብቻ ሳይሆን እሳቸው እንዳሸነፉ የገለጹት ሞንዳኔ ፥ የግድያ ሙከራ ጭምር ተደርጎባቸው እንዳመለጡ ገልጸዋል።
ጠበቃቸው መገደላቸውንም ጠቁመዋል።
አሁን ላይም ሀገር ውስጥ እንደማይገኙ ተነግሯል።
ዛሬ በዋና ከተማይቱ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የተቆጡ ሰልፈኞች " ስልጣን ለህዝብ " ፣ " ውድቀት ለፍሬሊሞ " እና " ፍሬሊሞ መውደቅ አለበት " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ተጠቅመው ሰልፉን በትነዋል።
አንድ እድሜያቸው 55 የሆነ የ6 ልጆች እናት " አሁን ካልተነሳን ምንም ለውጥ አይመጣም " ሲሉ ተናግረዋል።
" የፍሬሊሞ ጀርባ የሚታይበት ጊዜው አሁን ነው " ብለዋል።
ህዝባዊ ተቃውሞው ከተባባሰ በኋላ የሀገሪቱ ተሰናባች ፕሬዝዳንት ፊሊፔ ኑዩሲ ትንፍሽ አላሉም።
የመከላከያ ሚኒስትራቸው ግን ወጥተው ወታደሩን እንደሚያሰማሩ እና ስልጣን በኃይል ለማያዝ ሙከራ እንዳይደረግ አስጠንቅቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ማሰባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
• 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ገዢ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ተቃውሞና አመጽ ቀስቅሷል።
በአፍሪካዊቷ ሀገር ሞዛምቢክ ባለፈው ወር ላይ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።
ለረጅም አመታት ስልጣን ላይ የቆየው ገዢ ፓርቲ ዕጩ ዳንኤል ቻፖ " ምርጫውን አሸነፉ " መባሉ ከፍተኛ ተቃውሞ እና አመጽ ቀስቅሶ ሰዎች ተገድለዋል።
የአደባባይ ተቃውሞዎችም እየተደረጉ ነው።
አወዛጋቢ ነው በተባለው ምርጫ አሸንፏል የተባለውን " ፍሬሊሞ " የተሰኘውን ገዢ ፓርቲ ለመቃወም ዛሬ ማፑቶ ላይ ሰልፍ የወጡ ብዙሃኑ ወጣቶችን የፀጥታ ኃይሎች የአስለቃሽ ጭስ እየተኮሱ ሲያሳድዱ ውለዋል።
ምርጫውን " አሸንፏል " የተባለው ፓርቲ 49 ዓመታት ስልጣን ላይ የቆየ ሲሆን የምርጫ ውጤቱ የ49 ዓመታት ስልጣኑን ለማራዘም ያስችለዋል ተብሏል።
ይሄ ገዢ ፓርቲ እ.ኤ.አ ከ1975 ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛል።
የፍሬሊሞ ፓርቲ ዕጩ ምርጫ ማሸነፉ ይፋ ከተደረገ በኃላ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ 18 ሰዎች በፖሊስ መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተቋማት ገልጸዋል።
ምርጫው ከፍተኛ ፉክክር የተደረገበት ነበር የተባለ ሲሆን ብዙሃኑ ወጣቶች ዋነኛውን ተቀናቃኝ የ ' ፖዴሞስ ' መሪ ቬንሢዮ ሞንዳኔ ደግፈው ድምጽ መስጥታቸው ተነግሯል።
እሳቸውም ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ገልጸው ተቃውሞዎችን አበረታተዋል።
ምርጫው መጭበርበሩን ብቻ ሳይሆን እሳቸው እንዳሸነፉ የገለጹት ሞንዳኔ ፥ የግድያ ሙከራ ጭምር ተደርጎባቸው እንዳመለጡ ገልጸዋል።
ጠበቃቸው መገደላቸውንም ጠቁመዋል።
አሁን ላይም ሀገር ውስጥ እንደማይገኙ ተነግሯል።
ዛሬ በዋና ከተማይቱ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የተቆጡ ሰልፈኞች " ስልጣን ለህዝብ " ፣ " ውድቀት ለፍሬሊሞ " እና " ፍሬሊሞ መውደቅ አለበት " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ተጠቅመው ሰልፉን በትነዋል።
አንድ እድሜያቸው 55 የሆነ የ6 ልጆች እናት " አሁን ካልተነሳን ምንም ለውጥ አይመጣም " ሲሉ ተናግረዋል።
" የፍሬሊሞ ጀርባ የሚታይበት ጊዜው አሁን ነው " ብለዋል።
ህዝባዊ ተቃውሞው ከተባባሰ በኋላ የሀገሪቱ ተሰናባች ፕሬዝዳንት ፊሊፔ ኑዩሲ ትንፍሽ አላሉም።
የመከላከያ ሚኒስትራቸው ግን ወጥተው ወታደሩን እንደሚያሰማሩ እና ስልጣን በኃይል ለማያዝ ሙከራ እንዳይደረግ አስጠንቅቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ማሰባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA







Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91991