" ህጻናት ፣ እናቶች፣ አሮጊቶች ፣ ሽማግሌዎች ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " - ነዋሪዎች
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/91839
Create:
Last Update:
Last Update:
" ህጻናት ፣ እናቶች፣ አሮጊቶች ፣ ሽማግሌዎች ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " - ነዋሪዎች
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA


Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91839