Telegram Group & Telegram Channel
#መገናኛ

" የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ ተጀምሯል ፤ ለገንቢው እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው 45 ቀናት ነው " - አቶ ጥራቱ በየነ

ከፍተኛ መጨናነቅ ባለበት " መገናኛ ' አካባቢ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ፣ መኪና የሚበዛበትና የሚገናኝበት ፣ እጅግ በርካታ እግረኞችም የሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ነው " መገናኛ " አካባቢ።

በዚህ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለ የመሬት ውስጥ ለውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መሰራት ጀምሯል።

ይህ ፕሮጀክት ከቦሌ ኤርፖርት እስከ መገናኛ ባለው የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።

ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ምን አሉ ?

" መገናኛ በጣም ብዙ ሰዎች ተሽከርካሪዎችም የሚገናኙበት በመሆኑ ከፍተኛ መጨናነቅ አለ።

ቀድም ብሎ የቀለበት መንገድ የሚባለው ስለነበር መንገዱ ለእግረኞች ማቋረጫ በቂ አልነበረም። በዚህም ህብረተሰቡ በርካታ ችግር እንዲያሳልፍ ሆኗል።

ይሄ ትልቅ ጎዳና እንደመሆኑ የሚሰራው እግረኞች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ሳይቸገሩ በመሬት ውስጥ መሻገር የሚችሉበት ነው።

የታክሲ መጫኛና ማውረጃ ተርሚናልም ይገነባል በማዶ በኩል። በሙልጌታ ህንጻ ስርም ሁለት ወለል ያለው ተርሚናል ይገነባል።

እግረኞች ከአንዱ ተርሚናል ወደሌላኛው ተርሚናል የሚገናኙት በመሬት ውስጥ ይሆናል።

ከላይ ምንም አይነት የሰው እንቅስቃሴ በማይኖርበት ወይም በኒቀንስበት ሁኔታ ነው እየሰራን ያለነው።

ገንቢው ተቋራጭ ይህንን ስራ እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው ጊዜ 45 ቀን ነው።

ትንሽ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል። ለ45 ቀናት መንገዱን ስንዘጋው የነዋሪዎች እና የመኪና እንቅስቃሴ በተለይ መገናኛ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት እንደመሆኑ ጫና መፍጠሩ አይቀርም።

ዛሬ የምንወስነው ውሳኔ ምናልባት ለወደፊቱ ለበርከታ ረጅም አመታት ዘላቂ መፍትሄ ይሆናል።

ለ45 ቀናት በ3 ሺፍት ነው የምንሰራው። ከዛም ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ ከሚሰሩት ኮንትራክተሮች ጋር ተግባብተናል " ብለዋል።


የግንባታ ስራውን የሚያማክረው ማነው ? ስራውን የሚያማክረው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ነው።

ኮርፖሬሽኑ " የመገናኛ እግረኛ መተለለፊያ ስራ በአይነቱ የተለየ እና ዘመናዊ ነው " ብሎታል።

ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የፅዳት ቦታዎችም ይሰራሉ ብሏል።

" ፕሮጀክቱን በተባለው በ45 ቀናት እንደሚያልቅ እርግጠኞች ነን ፤ 24 ሰዓት ነው የሚሰራው  ፣ በቂ ማሽነሪ አለ፣ በተጓዳኝ ብረትና ሌሎች ዥግጅቶች እየተደረጉ ነው " ሲል ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤኤምኤን ቲቪ መውሰዱን ይገልጻል።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/91763
Create:
Last Update:

#መገናኛ

" የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ ተጀምሯል ፤ ለገንቢው እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው 45 ቀናት ነው " - አቶ ጥራቱ በየነ

ከፍተኛ መጨናነቅ ባለበት " መገናኛ ' አካባቢ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ፣ መኪና የሚበዛበትና የሚገናኝበት ፣ እጅግ በርካታ እግረኞችም የሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ነው " መገናኛ " አካባቢ።

በዚህ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለ የመሬት ውስጥ ለውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መሰራት ጀምሯል።

ይህ ፕሮጀክት ከቦሌ ኤርፖርት እስከ መገናኛ ባለው የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።

ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ምን አሉ ?

" መገናኛ በጣም ብዙ ሰዎች ተሽከርካሪዎችም የሚገናኙበት በመሆኑ ከፍተኛ መጨናነቅ አለ።

ቀድም ብሎ የቀለበት መንገድ የሚባለው ስለነበር መንገዱ ለእግረኞች ማቋረጫ በቂ አልነበረም። በዚህም ህብረተሰቡ በርካታ ችግር እንዲያሳልፍ ሆኗል።

ይሄ ትልቅ ጎዳና እንደመሆኑ የሚሰራው እግረኞች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ሳይቸገሩ በመሬት ውስጥ መሻገር የሚችሉበት ነው።

የታክሲ መጫኛና ማውረጃ ተርሚናልም ይገነባል በማዶ በኩል። በሙልጌታ ህንጻ ስርም ሁለት ወለል ያለው ተርሚናል ይገነባል።

እግረኞች ከአንዱ ተርሚናል ወደሌላኛው ተርሚናል የሚገናኙት በመሬት ውስጥ ይሆናል።

ከላይ ምንም አይነት የሰው እንቅስቃሴ በማይኖርበት ወይም በኒቀንስበት ሁኔታ ነው እየሰራን ያለነው።

ገንቢው ተቋራጭ ይህንን ስራ እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው ጊዜ 45 ቀን ነው።

ትንሽ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል። ለ45 ቀናት መንገዱን ስንዘጋው የነዋሪዎች እና የመኪና እንቅስቃሴ በተለይ መገናኛ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት እንደመሆኑ ጫና መፍጠሩ አይቀርም።

ዛሬ የምንወስነው ውሳኔ ምናልባት ለወደፊቱ ለበርከታ ረጅም አመታት ዘላቂ መፍትሄ ይሆናል።

ለ45 ቀናት በ3 ሺፍት ነው የምንሰራው። ከዛም ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ ከሚሰሩት ኮንትራክተሮች ጋር ተግባብተናል " ብለዋል።


የግንባታ ስራውን የሚያማክረው ማነው ? ስራውን የሚያማክረው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ነው።

ኮርፖሬሽኑ " የመገናኛ እግረኛ መተለለፊያ ስራ በአይነቱ የተለየ እና ዘመናዊ ነው " ብሎታል።

ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የፅዳት ቦታዎችም ይሰራሉ ብሏል።

" ፕሮጀክቱን በተባለው በ45 ቀናት እንደሚያልቅ እርግጠኞች ነን ፤ 24 ሰዓት ነው የሚሰራው  ፣ በቂ ማሽነሪ አለ፣ በተጓዳኝ ብረትና ሌሎች ዥግጅቶች እየተደረጉ ነው " ሲል ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤኤምኤን ቲቪ መውሰዱን ይገልጻል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91763

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Launched in 2013, Telegram allows users to broadcast messages to a following via “channels”, or create public and private groups that are simple for others to access. Users can also send and receive large data files, including text and zip files, directly via the app.The platform said it has more than 500m active users, and topped 1bn downloads in August, according to data from SensorTower.

The S&P 500 slumped 1.8% on Monday and Tuesday, thanks to China Evergrande, the Chinese property company that looks like it is ready to default on its more-than $300 billion in debt. Cries of the next Lehman Brothers—or maybe the next Silverado?—echoed through the canyons of Wall Street as investors prepared for the worst.

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA