TIKVAH-ETHIOPIA
#የ97ተመዝጋቢዎች
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/91704
Create:
Last Update:
Last Update:
#የ97ተመዝጋቢዎች
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA



Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91704