#AddisAbaba
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/91484
Create:
Last Update:
Last Update:
#AddisAbaba
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ? ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ? " - ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ
የኮሪደር ስራው ላይ የሚነሱት ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
የአዲስ አበባ ከተማን ገጽታ ይቀይራል የተባለው የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
አሁን ላይ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ስራ በተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ ነው።
የአሁኑን ጨምሮ ከቀደመው (የተጠናቀቀው) ስራ ጋር በተያያዘ ግን ብዙ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አንድ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር። በዚህም ወቅት የተለያዩ ጥያቄዎች ተጠይቀዋል። ከንቲባዋን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን ተጠየቀ ? ምንስ ተመለሰ ?
በውይይቱ ተሳታፊ ከነበሩት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
አቶ አበበ " የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ይሄ የኮሪደር ልማትን አይቃወምም። እኛ የአሮጌ ከተማ ፍቅር የለብንም። ቡቱቶ የሆነ ከተማ ፍቅር የለብንም። urbanization እየሰፋ ነው የሚሄደው ፤ ከተሜነት እየሰፋ ሲሄድ የህዝብ ቁጥር ሲጨምር ከዓለም ጋር መዘመን አለብን። ምንም ጥርጥር የለውም። እኛም እኮ የምንዝናናበት ነው የተሰራው ኮሪደር። ነገር ግን የሚሰሩት ልማቶች የሚሰሩት ለሰው ነው ፤ ስለዚህ ምን ያክል ነው የተጠናው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በተጨማሪ ለከንቲባዋ ፦
➡ ለመሆኑ ከኮሪደር ስራ ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባ ህዝብ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የለም ? የአዲስ አበባ ህዝብ ኑሮ አያሳስበውም ? አሁን ያለበት የኑሮ ደረጃ አያሳስበውም ?
➡ የህዝቡን ኑሮ አይታችሁታል ?
➡ ' እዬዬም እኮ ሲደላ ነው ' ለምን ኑሮው አይታይም የህዝቡ ?
➡ ይሄ ማህበረሰብ ከኮሪደር ልማቱ ይልቅ የዕለት ጉርሱን ሸፍኖ የሚበላበት ነገር አያስፈልገውም ?
➡ ፒያሳ ተነሳ ጥሩ ስራ ተሰርቷል በጣም ውብ ነው ደስ ይላል ፤ የተሰራው ውስጥም ነው ተቀምጠን የምንወያየው ግን በዚህ ፍጥነት አልተቻኮለም ?
➡ በየመንገዱ የሚሰሩ ፣ ጀብሎ የሆነው የሚቸረችሩ ወጣቶች የት ሄዱ ? ሁሉም ነገር ዝግ ተደርጎባቸዋል። ... ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?
" የኮሪደር ስራ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል ወይ ? እንዲህ መቸኮልስ ለምን አስፈለገ ፤ በርካታ የከተማው ህዝብ ጥያቄዎች የሉም ወይ ? የሚለው መነሳቱ ጥሩ ነው።
የኮሪደር ልማት ስራ ሲሰራ ሌሎች ስራዎችና አገልግሎቶች ወደኃላ ተብለዋል ማለት አይደለም። አስማምተን ነው እየሰራን ያለነው።
በተናበበ መንገድ አቅደን ፤ ሌሊትም ቀንም ለመስራት ራሳችንን አሳምንነን ነው እየሰራን ያለነው። ስራም ተከፋፍለን ነው። ቢሮ ማገልገል ያለበት ቢሮ ነው። እኛም ሙሉ ጊዜያችን ኮሪደር ብቻ አይደለም። ኮሪደር እያስተባበርን ሌሎች ስራዎችም እንሰራለን።
የኑሮ ውድነት ተነስቷል ፤ ችግሩ ስለገባን ነው የአዲስ አበባ ህጻናት ባዶ ሰሃን ያለ ሃጢያታቸው ምግብ ሳይኖራቸው ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ተደርጎ ያለ እድሜያቸው እንዲዋሹ ያለ ጥፋታቸው ፤ ከመራባቸው በላይ ምግብ ያላቸው እንዲመስሉ ባዶ ሰሃን ይዘው ትምህርት ቤት የሚወደቁበትን ታሪክ አይደል እንዴ የቀየርነው ?
ለ800 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርም እናቀርባለን፣ ደብተርና የትምህርት ቁሳቁስ እናቀርባለን ፤ ምግብ በቀን ሁለት ጊዜ ጥዋት ቁርስ ይበላሉ ምሳቸውን በልተው ወደቤት ይሄዳሉ ፤ ቤት ውስጥ ያለውን ገመና ስለምናውቅ ነው።
ትውልድ መገንባት አለበት ሀገራቸውን እየጠሉ እያማረሩ ማደግ ስለሌለባቸው። የአዲስ አበባ እናቶችን የኑሮ ጫና በሚገባ አይተነው ነው። ጓዳቸውን አይተን ነው።
ሁለተኛ በየቦታው ቦታ አመቻችተን ከ190 በላይ የእሁድ ገበያ የፈጠርነው ከስግብግብ ነጋዴዎች ነዋሪዎችን ለማስጣል የሰራነው የኑሮ ውድነቱ ስለሚገባን አይደለም ?
እነኛህ የአዲስ አበባ ከተማ የመግቢያ በሮች ላይ 5 ትልልቅ የገበያ ማዕከላት በቢሊዮን ልክ እንደ ኮሪደር ልማት በፍጥነት የገነባነው የኑሮ ውድነት ጫናው ስለሚገባን አይደለም ? ለምን አልተደረገም ከዚህ በፊት።
ገበሬው ቀጥታ አምጥቶ ምርት እንዲሸጥ ደላላው ከመሃል እንዲወጣ አላደረግንም እንዴ ?
አረጋውያን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ማግኘት አቅቷቸው አልተመለከትንም ፤ ' ተረጂነትን ታስፋፋላችሁ ' እየተባለን ስንተች ትችቱን ወደጎን ብለን በቀን አንድ ጊዜ ምግብ የሚያገኙበትን 21 የምገባ ማዕከላት ገንብተን እየመገብን ነው።
ከመንግሥት በጀት ውጭ 30,000 ቤቶች ገንብተን በነጻ ድሆችን አንስተን ዝቅ ብለን ያስገባንበት የህግ ግዴት አለብን እንዴ ? 30,000 ከመንግሥት በጀት ውጭ ነው። ውሃ የሚያፈስባቸው ከመጸዳጃ ቤት ጋር የሚኖሩ አንስተን አስገብተናቸዋል።
የኮሪደር ስራ በሰራንበት 2016 ዓ/ም ላይ ብቻ 18,000 ከትንሽ ፕሮጀክቶች እስከ አድዋ ድረስ ሰርተን ለህዝባችን ክፍት አድርገናል። የት የት እንደሆኑ ዳታ እንሰጣለን ሂዱና እዩ።
አጠቃላይ የከተማው ችግር እና ያለንበት ጥልቅ ድህነት በ1 ፣ በ3 ፣ በ5 ዓመት ተስርቶ አያልቅም የዘመናትን ውዝፍ በአንድ ጊዜ አልጨረሳችሁም ከሆነ ትክክል አይደለም። ሊያልቅ አይችልም።
በአንድ በኩል እኚህን ቶሎ ቅረፉ በሌላ በኩል አትቸኩሉ አብሮ አይሄድም።
ኮሪደር ስራ በባለሞያዎች በደንብ ተጠንቶ ነው የተጀመረው። መነሻው መዋቅራዊ ፕላን ነው። ያጠናንባቸውን አካባቢዎች ዶክመንቱ ይፋዊ ስለሆነ ማየት ይቻላል። የፕላን ጥሰቱ ልክ የለውም።
በየሰፈሩ ያሉ የፍሳሽ መስመሮች የተዘጉ ናቸው፣ እሳት አደጋ ሲፈጠር እንኳን ገብተን ማጥፋት አቅቶናል። ይቃጠሉ ይለቁ ? ከቆሻሻ ጋር መኖር የኢትዮጵያውያን ክብር ይመጥናል ? ጠረኑን አይታችሁታል ? እንዲህ ባልናገር ጥሩ ነበር ግን እውነታው ይሄ ነው።
ሰው ፍሳሽ ከላይ እየወረደበት እንዲተኛ፣ እናቶች ቆጥ ላይ እንጀራ እንዲጋግሩ ፣ እናቶች ከስር ልጆቻቸውንና የልጅ ልጆቻቸውን ይዘው ያድራሉ ከላይ ቆጥ ሰርተው ያከራያሉ። እነዚህ አካባቢዎች ታሪካቸው ይኸው ነው።
ቤቶቹ አርጅተዋል። በጭቃና በእንጨት ነው የተሰሩት አረጁ ግዜያቸው አለፈ ወደቁ በቆርቆሮ ቢለበዱ፣ ላስቲክ ቢታሰርባቸው ችግር መከላከል አይችሉም።
ወቀሳ የምታነሱ ሰዎች ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ በሴት እህቶቻችን እና እናቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል ለምን አያማችሁም ? ወይስ አታውቁም ? የዜግነት ክብራችንን አይመጥንም ነበር። ስለዚህ ክብራችንን በሚመጥን መንገድ ማልማት ይገባል።
ወደው አልነበረም ከቆሻሻ ጋር ሲኖሩ የነበሩት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው መጥተው ያ እንዲቀጥል የሚቀርበው ጥያቄ ፍጹም ተቀባይነት የለውም።
- ገቢያችን እንዲያድግ
- የስራ እድል በስፋት እንዲፈጠር
- ዜጎች ንጹህ ፅዱ ቦታ እንዲገበያዩ፣ እንዲሰሩ ፣ እንዲኖሩ ለማስቻለው ስራዎችን እየሰራን ያለነው።
የምንቸኩለው ጊዜ ስለሌለን ነው። ጉስቁልና ድህነት ውስጥ ነው ያለነው። ውርደት አለ ከዚህ ውስጥ መውጣት አለብን። አንዳንዶች የኛ ኑሮ ሻል ስላለ የድሃው አይታየን ይሆናል ! ከዚህ በላይ እንቸኩላለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA


Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91484