Telegram Group & Telegram Channel
#ወላይታዞን

“ ከ1,000 በላይ መምህራንና የቢሮ ሠራተኞች የሐምሌ ደመዎዝ አልተከፈለንም ” - የወላይታ ዞን መምህራን 

“ በአራት ወረዳዎች ሙሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው ” - የዞኑ ትምህርት መምሪያ

በወላይታ ዞን የሚገኙ መምህራን የሐምሌ 2016 ዓ/ም ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው፣ በዚህም የትምህርት ሥራ ሙሉ ለሙሉ እንዳልተጀመረ መምህራኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ክፍያ አለመፈጸሙን ተከትሎ አብዛኛዎቹ መምህራን ለማስተማር ፈቃደኞች ባለመሆናቸው የመማር ማስተማር ሂደቱ እንደተስተጓጎለ ነው የገለጹት።

“ ከ1,000 በላይ መምህራንና የቢሮ ሠራተኞች የሐምሌ ደመወዝ አልተከፈለንም ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ እንኳን ደመወዝ ሳይከፈል ተከፍሏቸውም ኑሮውን መቋቋም እንዳልተቻሉ ባለስልጣናቱ በደንብ ሊረዱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ያልተከፈለውን ጨምሮ ከዚህ ወዲያ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲፈጸምላቸውም በአንክሮ ጠይቀዋል። 

ለምን ክፍያው አልተፈጸመም ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ  የጠየቃቸው የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዜ ጉደና ሙሉ ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው አምነው ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

“ አራት የወረዳዎች ላይ ሙሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው። የሐምሌ ወር ክፍያ ላልተፈጸመላቸውም ወረዳዎች ገቢ ሰብስበው እንዲከፍሉ እየተደረገ ነው።

ከዚህ በፊትም ይታወቃል ከበጀት ካሽ ጋር ተያይዞ ወላይታ ዞን ላይ የደመወዝ ችግር ነበር። አሁን ግን እሱ ተቀርፎ ከዚህ በኋላ ሁሉም ሠራተኞች ሙሉ ደመወዝ ያገኛሉ።

በዞኑ ወረዳዎች የሚጠቀሟቸው በርካታ እዳዎች ስላሉ የሐምሌን ደመወዝ ሰብስበው እንዲጠቀሙ የሚል አቅጣጫ ተቀምጦ በዛው መልክ እየተሰራ ነው ያለው።

የመምህራን ብቻ ሳይሆን ሁሉም የመንግስት ሠራተኞች ወረዳዎች ላይ ሙሉ ደመወዝ አላገኙም። ግን ክፍያቸው እስከ 70 ፐርሰንት የደረሰ፤ እየጨረሱ ያሉ ወረዳዎችም አሉ።

ከሞላ ጎደል ችግሮች እየተፈቱ ነው። የሐምሌ ደመወዝ ስላልተከፈለ በሚል አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የትምህርት ሥራን ለማስተጓጎል የሚሞከሩ ሙከራዎች አሉና እሱ ተገቢ አይደለም።

አለመከፈሉ ስህተት ነው ግን በተከፈለው ደመወዝ ሥራ መስራት ይገባል። እየሰሩ ይጠይቁ ”
ብለዋል።

በዞኑ የመምህራንን ጨምሮ የሌሎችም የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ አለመፈጸም በተደጋጋሚ ማጋጠሙ የሚታወቅ ሲሆን ሠራተኞቹ የከፋ ችግር ለማሳለፍ እንደገደዱ እንደሆነ ከዚህ ቀደምም ሲያማርሩ ነበር።
 
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/91435
Create:
Last Update:

#ወላይታዞን

“ ከ1,000 በላይ መምህራንና የቢሮ ሠራተኞች የሐምሌ ደመዎዝ አልተከፈለንም ” - የወላይታ ዞን መምህራን 

“ በአራት ወረዳዎች ሙሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው ” - የዞኑ ትምህርት መምሪያ

በወላይታ ዞን የሚገኙ መምህራን የሐምሌ 2016 ዓ/ም ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው፣ በዚህም የትምህርት ሥራ ሙሉ ለሙሉ እንዳልተጀመረ መምህራኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ክፍያ አለመፈጸሙን ተከትሎ አብዛኛዎቹ መምህራን ለማስተማር ፈቃደኞች ባለመሆናቸው የመማር ማስተማር ሂደቱ እንደተስተጓጎለ ነው የገለጹት።

“ ከ1,000 በላይ መምህራንና የቢሮ ሠራተኞች የሐምሌ ደመወዝ አልተከፈለንም ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ እንኳን ደመወዝ ሳይከፈል ተከፍሏቸውም ኑሮውን መቋቋም እንዳልተቻሉ ባለስልጣናቱ በደንብ ሊረዱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ያልተከፈለውን ጨምሮ ከዚህ ወዲያ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲፈጸምላቸውም በአንክሮ ጠይቀዋል። 

ለምን ክፍያው አልተፈጸመም ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ  የጠየቃቸው የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዜ ጉደና ሙሉ ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው አምነው ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

“ አራት የወረዳዎች ላይ ሙሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው። የሐምሌ ወር ክፍያ ላልተፈጸመላቸውም ወረዳዎች ገቢ ሰብስበው እንዲከፍሉ እየተደረገ ነው።

ከዚህ በፊትም ይታወቃል ከበጀት ካሽ ጋር ተያይዞ ወላይታ ዞን ላይ የደመወዝ ችግር ነበር። አሁን ግን እሱ ተቀርፎ ከዚህ በኋላ ሁሉም ሠራተኞች ሙሉ ደመወዝ ያገኛሉ።

በዞኑ ወረዳዎች የሚጠቀሟቸው በርካታ እዳዎች ስላሉ የሐምሌን ደመወዝ ሰብስበው እንዲጠቀሙ የሚል አቅጣጫ ተቀምጦ በዛው መልክ እየተሰራ ነው ያለው።

የመምህራን ብቻ ሳይሆን ሁሉም የመንግስት ሠራተኞች ወረዳዎች ላይ ሙሉ ደመወዝ አላገኙም። ግን ክፍያቸው እስከ 70 ፐርሰንት የደረሰ፤ እየጨረሱ ያሉ ወረዳዎችም አሉ።

ከሞላ ጎደል ችግሮች እየተፈቱ ነው። የሐምሌ ደመወዝ ስላልተከፈለ በሚል አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የትምህርት ሥራን ለማስተጓጎል የሚሞከሩ ሙከራዎች አሉና እሱ ተገቢ አይደለም።

አለመከፈሉ ስህተት ነው ግን በተከፈለው ደመወዝ ሥራ መስራት ይገባል። እየሰሩ ይጠይቁ ”
ብለዋል።

በዞኑ የመምህራንን ጨምሮ የሌሎችም የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ አለመፈጸም በተደጋጋሚ ማጋጠሙ የሚታወቅ ሲሆን ሠራተኞቹ የከፋ ችግር ለማሳለፍ እንደገደዱ እንደሆነ ከዚህ ቀደምም ሲያማርሩ ነበር።
 
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/91435

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

If riding a bucking bronco is your idea of fun, you’re going to love what the stock market has in store. Consider this past week’s ride a preview.The week’s action didn’t look like much, if you didn’t know better. The Dow Jones Industrial Average rose 213.12 points or 0.6%, while the S&P 500 advanced 0.5%, and the Nasdaq Composite ended little changed.

In many cases, the content resembled that of the marketplaces found on the dark web, a group of hidden websites that are popular among hackers and accessed using specific anonymising software.“We have recently been witnessing a 100 per cent-plus rise in Telegram usage by cybercriminals,” said Tal Samra, cyber threat analyst at Cyberint.The rise in nefarious activity comes as users flocked to the encrypted chat app earlier this year after changes to the privacy policy of Facebook-owned rival WhatsApp prompted many to seek out alternatives.TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA