Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-86496-86497-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/86496 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትክክለኛ ፍትህ እንሻለን " - የቀድሞው የሀዋሳ ከንቲባ ቤተሰቦች

ላለፉት 5 ወራት በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር  ጸጋዬ ቱኬ ቤተሰቦች ፥ " በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።

የቀድሞው ከተንቲባ ወንድም እንደሆኑ የገለጹት አቶ አስፋዉ ቱኬ ፤ " ወንድሜ በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ያሉ ሲሆን  " በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ምን ያክል ህዝባዊ አመራር እንደነበርና ከሙስና የጸዳ ሰው እንደሆነ ሙሉ የሲዳማም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቃል " ብለዋል።

" በዚህ ንጽህናዉ ስለሚተማመንም ነበር ከሀገር ከወጣ በኋላ ወደሀገር ተመልሶ ለእስር የተዳረገው " ሲሉ አክለዋል።

አቶ አስፋው ፥ " ላለፉት አምስት (5) ወራት ፍትህ ተስተጓጉሎበትና የህክምና አገልግሎት አጥቶ ከፍርድ ቤት ፍርድ ቤት እየተመላለሰ ነው " ያሉ ሲሆን " አሁን ላይ የቀረበበት ክስም እሱ ከሀገር በወጣበት ወቅት በተወሰደዉ የመንግስት ቤት ውስጥ በነበሩና ጠፉ በተባሉ  ተራ የምንጣፍና የመጋረጃና መሰል የቤት እቃዎች ተጠያቂ መሆኑ እሱን በእስር ለማቆየት ብቻ የታሰበ ይመስላል "  ብለዋል።

" ከመምህርነት አንስቶ ሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ባገለገለበት ወቅት ያሳያቸዉ ቀና የህዝብ ፍቅር የልማት ወጤቶችና የመልካም አስተዳደር ፍሬዎች እንዲሁም በከተሞች መድረክ ያሳየዉ ከፍተኛ ውጤት በሲዳማም ሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የሚያስመሰግኑትና የሚያሸልሙት እንጅ የሚያሳስሩት አልነበሩም " ብለዋል።

አቶ አስፋው ቱኬ ፥ ወንድማቸው በጤና ችግር እየተሰቃዩ እንደሆነ በመግለጽ ቤተሰቡ ትክክለኛ ፍትህ እንደሚሻ ፤ የሚመለከተው አካል ሁሉ ይሄን ተማጽኗቸው እንዲሠማ ጥሪ አቅርበዋል።

የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ፥ በስልጣን ጊዜያቸው በሙስና ወንጀል እንዲሁም በከተማው ውስጥ ብልሹ አሰራር እንዲንሰራፋ አድርገዋል በሚል ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገው መታሰራቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/86496
Create:
Last Update:

" ትክክለኛ ፍትህ እንሻለን " - የቀድሞው የሀዋሳ ከንቲባ ቤተሰቦች

ላለፉት 5 ወራት በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር  ጸጋዬ ቱኬ ቤተሰቦች ፥ " በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።

የቀድሞው ከተንቲባ ወንድም እንደሆኑ የገለጹት አቶ አስፋዉ ቱኬ ፤ " ወንድሜ በፍትህ እጦት እየተንገላታ ነው " ያሉ ሲሆን  " በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ምን ያክል ህዝባዊ አመራር እንደነበርና ከሙስና የጸዳ ሰው እንደሆነ ሙሉ የሲዳማም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቃል " ብለዋል።

" በዚህ ንጽህናዉ ስለሚተማመንም ነበር ከሀገር ከወጣ በኋላ ወደሀገር ተመልሶ ለእስር የተዳረገው " ሲሉ አክለዋል።

አቶ አስፋው ፥ " ላለፉት አምስት (5) ወራት ፍትህ ተስተጓጉሎበትና የህክምና አገልግሎት አጥቶ ከፍርድ ቤት ፍርድ ቤት እየተመላለሰ ነው " ያሉ ሲሆን " አሁን ላይ የቀረበበት ክስም እሱ ከሀገር በወጣበት ወቅት በተወሰደዉ የመንግስት ቤት ውስጥ በነበሩና ጠፉ በተባሉ  ተራ የምንጣፍና የመጋረጃና መሰል የቤት እቃዎች ተጠያቂ መሆኑ እሱን በእስር ለማቆየት ብቻ የታሰበ ይመስላል "  ብለዋል።

" ከመምህርነት አንስቶ ሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ባገለገለበት ወቅት ያሳያቸዉ ቀና የህዝብ ፍቅር የልማት ወጤቶችና የመልካም አስተዳደር ፍሬዎች እንዲሁም በከተሞች መድረክ ያሳየዉ ከፍተኛ ውጤት በሲዳማም ሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የሚያስመሰግኑትና የሚያሸልሙት እንጅ የሚያሳስሩት አልነበሩም " ብለዋል።

አቶ አስፋው ቱኬ ፥ ወንድማቸው በጤና ችግር እየተሰቃዩ እንደሆነ በመግለጽ ቤተሰቡ ትክክለኛ ፍትህ እንደሚሻ ፤ የሚመለከተው አካል ሁሉ ይሄን ተማጽኗቸው እንዲሠማ ጥሪ አቅርበዋል።

የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ፥ በስልጣን ጊዜያቸው በሙስና ወንጀል እንዲሁም በከተማው ውስጥ ብልሹ አሰራር እንዲንሰራፋ አድርገዋል በሚል ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገው መታሰራቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/86496

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA