Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-79671-79672-79673-79674-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/79673 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
ልዑካን ቡድኑ በመቐለ የሚኖረው ቆይታ ምን ይመስላል ? ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተመራ የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክሳዊት ቤተክርስትያን ሲኖዶስ ልኡክ ዛሬ ጥዋት መቐለ ገብቷል። ቆይታው ለሁለት ቀን ይሆናል።  ለልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ አቀባበል ተደርጓል። ቀጥሎ በመቐለ ቅዱስ ሚካኤል…
#Update

ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ መቐለ ትግራይ ሲደርሱ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካብኔ ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ በትግራይ ጊዚያዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ በተለያዩ ማህበራትን የማህበረሰብ ወኪሎች እና ወጣት ዘማርያን ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ በመርኃግብሩ ቢገለጽም በስፍራው የትግራይ ክልል የሃይማኖት አባቶች ፣ ዘማርያን #እንዳልተገኙ ለማወቅ ተችሏል።

በመቀጠል ልዑኩ በክልሉ በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች እገዛ የሚውል 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በፕላኔት ሆቴል በተደረገ መርኃግብር ላይ ያስረከበ ሲሆን በትግራይ ያሉ የሃይማኖት አባቶች ግን በሥፍራው አልታደሙም።

ደጋፉን የተቀበሉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከቅድስት ቤተከርስትያንዋ የተበረከተውን ድጋፍ የዘገየ ቢሆንም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

በቅዱስ ሲኖዶሱና በትግራይ አብያተ ክርስትያናት አባቶች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ከተካሄደው ጦርነት ተያይዞ አንዳንድ ጳጳሳት ባደረጉዋቸው ከሃይማኖት ያፈነገጡ ንግግሮች ግንኙነቱ እንዲሻከር ምክንያት መሆኑና፤ ይህን ቅሬታ የፈጠረው አለመግባባት በመመካከር በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የረፈደ ቢሆንም የሚደገፍ ነው ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም ፥ ቅዱስ ሲኖዶሱ ቤተከርስትያንዋ በጀመረችው ጥረት የወደሙ ቤተእምነቶችን ከመገንባትና የተጎዱ የሃይማኖት አባቶች ከመደገፍ በዘለለ የተፈጠረው መቃቃር እንዲሻር በልዩ ጥንቃቄና ፅናት በመስራት ግንኙቱ ተሻሽሎ ትክክለኛ መንፈሳዊ ሂወት እንዲቀጥል ለማድረግ በሚሰራው ስራ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት ቃል በትግራይ የተካሄደው ጦርነት ለማቆም ቅዱስ ሲኖዶሱ በግዜው ድምፁ ባለማሰማቱ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል ፣ ይቅርታው የበለጠ እንዲጠናከር ውይይት እጅግ አሰፈላጊ መሆኑ በመገንዘብ የትግራይ የሃይማኖት አባቶች ተባባሪ እንዲሆኑ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል።

ያለፈው ዘግናኝና አሳፋሪ ጦርነት ለማቆም የትግራይና የፌደራል መንግስት ሃላፊዎች በፕሪቶሪያ የፈረሙት ስምምነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የሃይማኖት አባቶች ይህንን ፈለግ ተከትለው  በመወያየት መግባባት እና አንድነት መፍጠር ይገባቸዋል ብለዋል።

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በተመራው የሰላም ልዑክ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ አትሌት ደራርቱ ቱሉና ሌሎች ተገኝተዋል።

መረጃው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ አባል ነው።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/79673
Create:
Last Update:

#Update

ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ መቐለ ትግራይ ሲደርሱ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካብኔ ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ በትግራይ ጊዚያዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ በተለያዩ ማህበራትን የማህበረሰብ ወኪሎች እና ወጣት ዘማርያን ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ በመርኃግብሩ ቢገለጽም በስፍራው የትግራይ ክልል የሃይማኖት አባቶች ፣ ዘማርያን #እንዳልተገኙ ለማወቅ ተችሏል።

በመቀጠል ልዑኩ በክልሉ በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች እገዛ የሚውል 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በፕላኔት ሆቴል በተደረገ መርኃግብር ላይ ያስረከበ ሲሆን በትግራይ ያሉ የሃይማኖት አባቶች ግን በሥፍራው አልታደሙም።

ደጋፉን የተቀበሉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከቅድስት ቤተከርስትያንዋ የተበረከተውን ድጋፍ የዘገየ ቢሆንም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

በቅዱስ ሲኖዶሱና በትግራይ አብያተ ክርስትያናት አባቶች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ከተካሄደው ጦርነት ተያይዞ አንዳንድ ጳጳሳት ባደረጉዋቸው ከሃይማኖት ያፈነገጡ ንግግሮች ግንኙነቱ እንዲሻከር ምክንያት መሆኑና፤ ይህን ቅሬታ የፈጠረው አለመግባባት በመመካከር በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የረፈደ ቢሆንም የሚደገፍ ነው ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም ፥ ቅዱስ ሲኖዶሱ ቤተከርስትያንዋ በጀመረችው ጥረት የወደሙ ቤተእምነቶችን ከመገንባትና የተጎዱ የሃይማኖት አባቶች ከመደገፍ በዘለለ የተፈጠረው መቃቃር እንዲሻር በልዩ ጥንቃቄና ፅናት በመስራት ግንኙቱ ተሻሽሎ ትክክለኛ መንፈሳዊ ሂወት እንዲቀጥል ለማድረግ በሚሰራው ስራ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። 

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት ቃል በትግራይ የተካሄደው ጦርነት ለማቆም ቅዱስ ሲኖዶሱ በግዜው ድምፁ ባለማሰማቱ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል ፣ ይቅርታው የበለጠ እንዲጠናከር ውይይት እጅግ አሰፈላጊ መሆኑ በመገንዘብ የትግራይ የሃይማኖት አባቶች ተባባሪ እንዲሆኑ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል።

ያለፈው ዘግናኝና አሳፋሪ ጦርነት ለማቆም የትግራይና የፌደራል መንግስት ሃላፊዎች በፕሪቶሪያ የፈረሙት ስምምነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የሃይማኖት አባቶች ይህንን ፈለግ ተከትለው  በመወያየት መግባባት እና አንድነት መፍጠር ይገባቸዋል ብለዋል።

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በተመራው የሰላም ልዑክ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ አትሌት ደራርቱ ቱሉና ሌሎች ተገኝተዋል።

መረጃው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ አባል ነው።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/79673

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has exploded as a hub for cybercriminals looking to buy, sell and share stolen data and hacking tools, new research shows, as the messaging app emerges as an alternative to the dark web.An investigation by cyber intelligence group Cyberint, together with the Financial Times, found a ballooning network of hackers sharing data leaks on the popular messaging platform, sometimes in channels with tens of thousands of subscribers, lured by its ease of use and light-touch moderation.

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

TIKVAH ETHIOPIA from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA