tg-me.com/rituaH/1587
Last Update:
"+"ነገረ ሃይማኖት"+"
የነገረ ሃይማኖት ትምህርት አጠር ተደርጎ የቀረበ፡-
ክፍል ፩
........ ....... ...... ...... ...... ...... ...... ..........
ሃይማኖት እምነትና መታመን
................ .. ... ... ..... . . ........ ... ..........
"+"ሃይማኖት"+"
ሃይማኖት ማለት ምን ማለት ነው?
+ ሃይማኖት ማለት "ሃይመነ" ከሚለው የግእዝ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜውም "ማመን መታመን" ማለት ነው፡፡
ሃይማኖት ምንድነው?
+ ሃይማኖት እግዚአብሔር ራሱን ለሰው ልጅ የገለጠው መገለጥ ነው። እግዚአብሔር ባህሪው ረቂቅ አኗኗሩ ምጡቅ ስለሆነ የሰውም ሆነ የመላዕክት አእምሮ ተመራምሮ ሊደርስበትና ባሕሪው እንዲህ ያለነው አኗኗሩ እንዲህ ያለነው ይህን ይመስላል ሊለው የማይችለው ነው።እርሱ በጊዜና በቦታ የማይወሰን ዘላለማዊና ምሉዕ ሲሆን ፍጥረቱ ግን በጊዜና በቦታ የተወሰነ ስለሆነ ውስኑ የማይወሰነውን ሊየውቀውና በምርምር ሊደርስበት አይችልም።
.
ሆኖም ግን ምንምእንኲዋ እግዚአብሔር በባርሪውና በአኗኗሩ በራሱ ብቻ የሚታወቅ ረቂቅ አምላክ ቢሆንም እኛ ፈጽመን የማናውቀው እና ስለ እርሱ ምንም ፍንጭ የሌለን ሆነን እንድንቀር አልተወንም። ከቸርነቱ የተነሳ አቅማችን ሊረዳው በሚችለው መጠን ማንነቱን፣ህላዌውን ፣ባህሪውን፣ መግቦቱን፣ ፈታሒነቱን፣ ፈቃዱን... እናውቅ ዘንድ በተለያየ መጠን ገልጦልናል። ሃይማኖት የሚባለው ይህ እግዚአብሔር በራሱ ፈቃድ እናውቀው ዘንድ ስለራሱ የገለጠው መገለጥ ነው።ስለሆነም ሃይማኖት እግዚአብሔር ራሱን ለእኛ ያሳየበት መንገድ፣የሰው ልጅ ሊቀበለው በሚችለው መጠን ስለራሱ ማንነት ለእኛ የገለጠው እውነታ ነው።
.
እግዚአብሔር አንድ ስለሆነ፣ባህሪውም የማይለወጥ ስለሆነ ሃይማኖት አንድና የማይለወጥ ነው። ስለዚህም ሊኖር የሚችለው ብቸኛ ሃይማኖት አንድ ብቻ!ነው። ብዙ ሃይማኖቶች አሉ ማለት ግን ወይ እግዚአብሔር በተለያየ ጊዜ የተለያየ ነገር ይናገራል ማለትን፣ አለዚያም ደግሞ ባህሪው ይለዋወጣል የሚለውን ያስከትላል፤ ሆኖም እነዚህ አነጋገሮች ለእግዚአብሔር ሊነገሩ ቀርቶ ፍጹም ጸያፎች ናቸው። እርሱ በተለያየ ጊዜ እርስ በእርሱ የሚቃረን የተለያየ ነገ አይናገርምና። መለወጥ የፍጡር ባህሪ እንጂ የፈጣሪ አይደለምና። ስለዚህ ሃይማኖት እንድ ብቻ ነው።መጽሐፍ ቅዱስም"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" የሚለው ለዚህ ነው። ኤፌ ፬፥፭
... ይቀጥላል
…/…/…/…/…/…/…/…/…/……//…/…/………
በየእለቱ አጥንትን የሚያለመልሙ መንፈሳዊ ጽሁፎችን ለማግኘት ይቀላቀሉን፡-
👉 @rituaH @rituaH
👉 @rituaH @rituaH
👉@rituaH @rituaH
BY ርቱዓ ሃይማኖት
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/1587