tg-me.com/rituaH/1539
Last Update:
ላው ገዥ፤ ከአንዱም ሊቀ
ካህናት ወደ ሌላው ሊቀ ካህናት እያመላለሱት በሐሰት ሲከሱትና ሲያስመሰክሩበት፤ ሲኮንኑትና ሲወነጅሉት አድረው ዐርብ ጧት ወደ ገዥው ወደ ጲላጦስ ዘንድ ቀርቦ ሞት የማይገባው አምላክ በግርግር፣ በተድእኖና በጩኸት ብዛት በመስቀል ላይ ተሰቅሎ እንዲሞት የተወሰነበት በመሆኑ በዚሁ በዕለተ ዓርብ በቀትር ጊዜ ስድሰት ሰዓት
ሲሆን በግራና በቀኝ ሁለት ወንጀለኞች፣ ምንም ወንጀልና በደል የሌለበት ንጹሐ ባሕርይ ክርስቶስ ያላንዳች ጥፋት እንደወንጀለኛ ተቆጥሮ በወንበዴዎች መካከል በመስቀል ላይ ተሰቅሏል፡፡ ከ6 -9 ሰዓትም በመስቀል ላይ ሆኖ ብዙ ተአምራትን ሲፈጽምና ለሰው ሁሉ ትምህርት ሰጭ የሆኑ ቃላትን ሲናገር ከቆየ በኋላ በ9 ሰዓት ተጠማሁ ሲላቸው ያቀረቡለትን መራራ ሐሞትና ከርቤ ከቀመሰ በኋላ ተፈጸመ የሚለውን የመጨረሻ ቃል ተናግሮ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለይቶ በራሱ ፈቃድ የመጣበትን የማዳን ሥራ ፈጽሞአል፡፡
ክርስቶስ በሰሙነ ሕማማቱና በዕለተ ስቅለቱ የተቀበላቸው ፀዋትወመከራዎች እጅግ በጣም ብዙዎች እንደሆኑ ከቅዱሳት መጻሕፍት
መረዳት የሚቻል ሲሆን በተለይ በግብረ ሕማማቱና ድርሳነ ማሕየዊ በተሰኙ መጻሕፍት በዝርዝር ተገልጠው ይገኛሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ
13ቱ ሕማማተ መስቀል የተሰኙት ጥቂቆቹ ናቸው እነሱም ተአስሮ ድኅሪት፤ ተስሕቦ በሐብል፤ ወዲቅ ውስተ ምድር፤ ተከይዶ በእግረ አይሁድ፤ ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ፤ ተጸፍኦ መልታሕት፤ ተቀስፎ ዘባን፤
ተኮርዖተ ርእስ፤ አክሊለ ሶክ፤ ፀዊረ መስቀል፤ ተቀንዎ በቅንዋት፤ ተሰቅሎ በዕፅና ሰሪበ ሐሞት ናቸው፡፡
መድኃኒታችን በዕፀ መስቀል ላይ እያለ ዐርብ ከ6 እስከ 9 ሰዓት ባለው ጊዜ 7 ተአምራት ተደርገዋል፡፡
1.ፀሐይ ጨልሞአል፤
2.ጨረቃ ደም ሆኖአል፤
3.ከዋክት ረግፈዋል፤
4.አለቶች (ድንጋዮች) ተፈረካክሰዋል፤
5.መቃብራት ተከፍተዋል፤
6.ሙታን ተነሥተዋል፤
7.የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ማንም ሳይነካው ራሱ ተቀዷል፡፡
ቅዳሜ፡-ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአካለ ሥጋ በመቃብር
ውስጥ ነበር፤ መቃብሩም በዘብ ይጠበቅ ነበር፡፡ ክርስቶስ በአካለ ሥጋ
ከዐርብ 11 ሰዓት እስከ እሁድ መንፈቀ ሌሊት ድረስ በመቃብር ውስጥ የነበረ ሲሆን በአካለ ነፍስ ደግሞ ወደ ሲዖል ወርዶ ከአዳም ጀምሮ
በሲዖል ውስጥ ለነበሩ ነፍሳት ነፃነትን ሰብኮላቸዋል፡፡ ከሲዖል ወጥተው ወደ ገነት እንዲገቡ አድርጓቸዋል፡፡ በአጠቃላይ እስከ ክርስቶስ ሞት ድረስ በፍርድ ግዞት ውስጥ ያሉትን ሁሉ በመከራውና በሞቱ ድል አጎናጽፎአቸዋል፡፡ በኃጢአት ባርነት ውስጥ የነበሩት ሁሉ ሙሉ ነፃነትን አግኝተው የእግዚአብሔርን መንግስት የመውረስ ዕድልን አግኝተዋል፡፡
(በሊቀ ብርሃናት ኢሳይያስ ወንድምአገኘሁ)
ምንጭ:- መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ገፅ
BY ርቱዓ ሃይማኖት
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/1539