tg-me.com/rituaH/1516
Last Update:
“ሀገራዊ የጸሎት ጥሪ እንጂ ጾም አልተባለም”
ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖተ ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ
መጋቢት 28/2012 ዓ/ም
የኮሮና ቫይረስ በሀገራችን መከሰቱን ተከትሎ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አአባቶች በአንድ ላይ ሆነው ብሔራዊ የጸሎት አዋጅ ትናንተ በ27/07/2012 ዓ.ም ማወጃቸው የሚታወስ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የታወጀው የጸሎት አዋጅ ሆኖ እያለ በተለያዩ የማኀበራዊ ድረ ገጾች ለምዕመናን የተሳሳተን መረጃ የሰጡ መሆናቸውን ያነሱት ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ተደለ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች ያወጁት ለሁሉም ሃይማኖቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ብሔራዊ የጸሎትና የንሥሓ አዋጅ እንጅ የጾም አይደለም ብለዋል፡፡
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጾም መሠረት ከትንሣኤ እስከ በዓለ ሃምሳ የጾም ሥርዓት እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማቱ ጉባኤ በማንኛምው ቤተ እምነት ሕግና ሥርዓት ጣልቃ የማይገባ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ እንደማይችል ጨምረው ገልጠዋል ፡፡
አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሆነ የሌሎች አብያተ እምነት የጋራ ጸሎትና በኮሮና ወረርሽኝ እና መሰል ጉዳዮች የትምህርትና የጸሎት መርሐ ግብር በአራት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከዛሬ ማለትም ከ28/07/2012 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00-4፡00 ለተመልካች እንደሚደርስ ገልጠው ሁሉም እንዲከታተል ጠቁመዋል ፡፡
በመጨረሻም ጠቅላይ ጸሓፊው ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ በዘመናችን የተከሰተው ክፉ ወረርሽኝ በሽታ እንዲወገድ ሁላችንም በበረታ ክንድ ልንጸል ይገባልም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመርሐ ግብር ተራ በአራቱ ጣቢያዎች
ሰኞ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ማክሰኞ፡በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ረቡዕ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ሐሙስ፡ በ WALTA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
አርብ ፡ በ ETV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
ቅዳሜ፡ በ FANA ከምሽቱ 3፡00-4፡00
እሑድ፡ በ ADDIS TV ከምሽቱ 3፡00-4፡00
©EOTC TV
BY ርቱዓ ሃይማኖት
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/1516