Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Yecampas_Hiwet/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
የካምፓስ ህይወት_MAHIR | Telegram Webview: Yecampas_Hiwet/6821 -
Telegram Group & Telegram Channel
​​​​╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
." ከራስ ሽሽት ".
. ( ሶፊያ አህመድ )

╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝

. በ @tibebislam_nw የቀረበ
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ
.━─━────༺༻────━─━


.ክፍልስድስት...⓺
「✿」────❮✿



አባታቸው አቶ ጀማል ወደውስጥ እንደገባ ከኋላው አንድ በወጣቶች የእድሜ ክልል ውስጥ ያለ ፣ የተስተካከለ ቁመትና ሰውነት ያለው ቀላ ያለ ልጅ ተከትሎት ገባ። አልይን አቅፎ ሰላም ካለው በኋላ መርየምን ፣ ፈቲንና ሀዩን በርቀት ሰላምታ ሰቷቸው ከአባትየው አጠገብ ሄዶ ቁጭ አለ።

ሉቅማን ይባላል...እዚ እኛው ሰፈር እኮ ነው ያለው...ወደአስፓልቱ መውጫ ጋር ያለው ትልቅ ህንፃ የሱ ነው...እንዴት ያለ መልካም ሰው መሰላቹ...በማለት አባትየው ስለወጣቱ በአጭሩ ገለፀላቸው።
ስለሉቅማን ሲያወራ በጣም ደስ እያለው ነው። ሉቅማንም ስለሱ ጥሩ ነገር ሲወራ እንደሚሽኮረመም ሰው አንገቱን ደፋ ያደርጋል።

ሀዩና ፈቲ ተነስተው ምግብ ማቀራረብ ጀመሩ። ሉቅማንና አቶ ጀማልም የቀለጠ ወሬ ይዘዋል። ስለንግድ ፣ ስለትዳር እያነሱ ተጫዋወቱ። ምግብ ቀርቦ አንድ ሁለት ከጎረሱ በኋላ ሉቅማን
በጣም ይጣፍጣል ቆንጆ ምግብ ነው...እያለ በቀስታ ወደሀዩ ተመለከተ።
ታድያስ እንዴ ልጄ እኮ ባለሙያ ነው... ሀዩ ናት የሰራችው...በምግብማ አትታማም! የሉቅማንን ትከሻ መታ መታ አደረጉት!

ምግብ በልተው ከጨረሱ በኋላ
በሉ ልጆች ወደጓዳ ገብታቹ ተጫወቱ በቃ ...እኔና ሉቅማን ትንሽ የምንጨዋወተው ነገር አለ... ብሎ ሁሉም እንዲገቡ ነገራቸው። ሀዩም ልጆቹን ይዛ ወደክፍላቸው ገባች።

*

ሀሰን እራሱን አሞት ሶፋ ላይ ተኝቷል። የሀዩን ስልክ በመጠበቅ እንቅልፍን ስለከዳ እየቀጣው ይመስላል።
ሀሰንዬ አሁንስ እንዴት ነህ ትንሽ አልተሻለህም? አለች የሀሰን እናት ልቧ እየተንሰፈሰፈ መጥታ አጠገቡ ቁጭ አለች።
ወይ ካልሆነ ሆስፒታል እንሂድ.. ሰውነቱን በእጇ ስትዳብሰው በጣም ያተኩሳል።
አይ ኡሚ እዚው ብሆን ይሻለኛል... አለመሄዱን ለማረጋገጥ አተኛኘቱን አመቻቸ።
ከትምህት ቤት ደውለው ነበር...አሞት ነው የቀረው ብያቸዋለው...
ሌላስ ምን አሉ?
ምንም...ሌላ ምን ይላሉ ልጄ?
አዲስ ተማሪ ገብቷል አላሉሽም? ሀሳቡ ሁሉ ሀዩ ጋር ስለሆነ እንጂ ከመች ጀምሮ ነው አዲስ ተማሪ ሲገባ ለወላጅ የሚነገረው። እናቱ በግርምት አፍጥጣ ስታየው ነው ምን እንዳላት ትዝ ያለው። ደነገጠ!
በቃ ኡሚ ልተኛ...ብተኛበት ይሻላል..አትጨነቂ አንቺ... ምንም እንዳትጠይቀው ፊቱን አዙሮ እንደሚተኛ ሰው አስመሰለ።

ሰው እንዴት አንድ ሰውን ለረጅም ጊዜ ከዛ ሰው ምንም አይነት የፍቅር ምላሽ ሳያገኝ ሊያፈቅር ይችላል? ያውም በዚ ጊዜ...ትናንት ተዋውቀው ዛሬ የሚጣሉ ሰዎች በበዙበት ዘመን.. ፍቅር ቃሉ ብቻ የቀረ በሚመስል ብዙዎቹ በፍቅር በሚቀልዱበት ዘመን...

ሀሰን እኮ የእውነት አፍቃሪ ነው። እሷን ያፈቀራት ገንዘብ አላት ብሎ ፣ ከሷ ጥቅምን ፈልጎ ወይም እሷ ትወደኛለች ብሎ አይደለም። በቃ ፍቅር የሚባለው ነገር በትክክል በልቡ ስለገባ ነው።
ሀሰን አሁንም ቢሆን ተስፋ አልቆረጠም። ስልኳ ካርድ ስለሌለው ይሆናል ወይም አልተመቻትም ይሆናል እያለ ዛሬም የሀዩን የስልክ ጥሪ እየጠበቀ ነው። ያልደወለችበትን መጥፎ ጎን ጭራሽ ማሰብ አልፈለገም።

*

ሀዩ አባታቸው ውስጥ ግቡ ብሏቸው ብትገባም ተረጋግታ ልትቀመጥ ግን አልቻለችም። ይሄን ያህል ስለምን ሊያወሩ ቢሆን ነው እንድንገባ ያደረጉን? በዛ ላይ ዛሬ ያለወትሮው የአባቷ ሙገሳ ፣ ፈገግታ ብቻ ብዙ ነገር ለየት ብሎባታል።
ልጆቹን ክፍል ካስገባች በኋላ ለሳሎኑ የምግብ መስሪያ ቤቱ ስለሚቀርብ እቃ እንደምታስቀምጥ መስላ ገብታ ጆሮዋን ወደሳሎኑ አስጠግታ ስለምን እንደሚያወሩ መስማት ጀመረች።

አባት፡ እቺት እንግዲ ...ቆንጆዋ የመጀመሪያ ልጄ ሀዩ ማለት እሷ ናት..

ሉቅማን፡ ማሻአላህ ቆንጅዬ ልጅ አለቾት...እና እሷስ ስለነገሩ ታውቃለች?

አባት፡ ኧረ አታውቅም... ዛሬ ጠዋት ነው እንደምትመጣ ብቻ የነገርኳቸው...ግን ልጄ አርቆ አሳቢ ናት...ቀድማ እንደምታስብ አልጠራጠርም...

አሁን ይባስ ለመስማማት ወደግድግዳው ተጠጋች። ስለምን እንደሚያወሩ ምንም ሊመጣላት አልቻለም።

ሉቅማን፡ ያው እንዳልኮት ነው...ካምፓስ እስከምትገባ ድረስ እዚው ሆና መማር ትችላለች...እኔ እሷን ጨምሮ ሁሉንም ልጆች አስተምራለሁ... ይሄ አመት አልቆ 12ተኛ ክፍልን ከጨረሰች በኋላ ግን ከእኔ ጋር እንድትኖር ነው የምፈልገው...

አባት፡ ኧረ ችግር የለውም...ሀያቴን እኔ አንድ ነገር ብያት እንቢ አትለኝም...በዛ ላይ የሚጠቅማትን በደንብ የምታውቅ ልጅ ናት...

አሁን ሁሉም ነገር ገባት። አባቷ ለሉቅማን ሊድራት እንደሆነ...በጣም ደነገጠች። ከወንድምና እህቶቿ ላለመነጠል ብላ ብዙ መስዋትነት ከፍላ ነበር እኮ። አሁንም ቢሆን እሷ ማግባት አትፈልግም።

ሉቅማን፡ እስከዛው ግን አደራዎትን እርሶ ሊጠብቋት ይገባል.. እስከነክብረንፅህናዋ ነው ላገባት የምፈልገው..

አባት፡ ኧረ ሀያቴ ወንድ ራሱ ጭራሽ አታውቅም እኮ...ለዚስ ጭራሽ አታስብ...

ሉቅማን፡ መርሀባ ያው ትምህርት ከተጀመረ ገና 1 ወር እንኳን ስላልሞላው ትምህርቷን አሁን መጀመር ትችላለች...

ሀዩ የምትገባበት ቀዳዳ ጠፋት። የምትይዝ የምትጨብጠውን አጣች። ለማታውቀና ለማትፈልገው ሰው ልትዳር ነው...መቀበል አትፈልግም።
በጭራሽ! በጭራሽ አላገባም! እልህ በተናነቀው የሲቃ ድምፅ ከሷ ውጪ ማንም በማይሰማ መልኩ ዝቅ አርጋ እየደጋገመች ተናገረች።
ያአላህ ስቃዬን አታብዛው...እኔ ደካማ ባርያህ ነኝ...ምንም ነገር ለመጋፈጥ አቅሙ የለኝም..ያ አላህ የልቤን አንተ ነህ የምታውቀው...በማልችለው ነገር አትፈትነኝ...እያለቀሰች እጇን ከፍ አርጋ ስሞታዋን ለአላህ አቀረበች።
ወይ ዱንያ ቀጣይስ ምን ይፈጠር ይሆን? አለች በልቧ ጭራሽ ያልጠበቀችው ነገር በመፈጠሩ ግራ እየተጋባች።

#ክፍል\ሰባት...⓻...ይቀጥላል
✿❯────「✿」─



tg-me.com/Yecampas_Hiwet/6821
Create:
Last Update:

​​​​╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
." ከራስ ሽሽት ".
. ( ሶፊያ አህመድ )

╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝

. በ @tibebislam_nw የቀረበ
. ልብ አንጠልጣይ ታሪክ
.━─━────༺༻────━─━


.ክፍልስድስት...⓺
「✿」────❮✿



አባታቸው አቶ ጀማል ወደውስጥ እንደገባ ከኋላው አንድ በወጣቶች የእድሜ ክልል ውስጥ ያለ ፣ የተስተካከለ ቁመትና ሰውነት ያለው ቀላ ያለ ልጅ ተከትሎት ገባ። አልይን አቅፎ ሰላም ካለው በኋላ መርየምን ፣ ፈቲንና ሀዩን በርቀት ሰላምታ ሰቷቸው ከአባትየው አጠገብ ሄዶ ቁጭ አለ።

ሉቅማን ይባላል...እዚ እኛው ሰፈር እኮ ነው ያለው...ወደአስፓልቱ መውጫ ጋር ያለው ትልቅ ህንፃ የሱ ነው...እንዴት ያለ መልካም ሰው መሰላቹ...በማለት አባትየው ስለወጣቱ በአጭሩ ገለፀላቸው።
ስለሉቅማን ሲያወራ በጣም ደስ እያለው ነው። ሉቅማንም ስለሱ ጥሩ ነገር ሲወራ እንደሚሽኮረመም ሰው አንገቱን ደፋ ያደርጋል።

ሀዩና ፈቲ ተነስተው ምግብ ማቀራረብ ጀመሩ። ሉቅማንና አቶ ጀማልም የቀለጠ ወሬ ይዘዋል። ስለንግድ ፣ ስለትዳር እያነሱ ተጫዋወቱ። ምግብ ቀርቦ አንድ ሁለት ከጎረሱ በኋላ ሉቅማን
በጣም ይጣፍጣል ቆንጆ ምግብ ነው...እያለ በቀስታ ወደሀዩ ተመለከተ።
ታድያስ እንዴ ልጄ እኮ ባለሙያ ነው... ሀዩ ናት የሰራችው...በምግብማ አትታማም! የሉቅማንን ትከሻ መታ መታ አደረጉት!

ምግብ በልተው ከጨረሱ በኋላ
በሉ ልጆች ወደጓዳ ገብታቹ ተጫወቱ በቃ ...እኔና ሉቅማን ትንሽ የምንጨዋወተው ነገር አለ... ብሎ ሁሉም እንዲገቡ ነገራቸው። ሀዩም ልጆቹን ይዛ ወደክፍላቸው ገባች።

*

ሀሰን እራሱን አሞት ሶፋ ላይ ተኝቷል። የሀዩን ስልክ በመጠበቅ እንቅልፍን ስለከዳ እየቀጣው ይመስላል።
ሀሰንዬ አሁንስ እንዴት ነህ ትንሽ አልተሻለህም? አለች የሀሰን እናት ልቧ እየተንሰፈሰፈ መጥታ አጠገቡ ቁጭ አለች።
ወይ ካልሆነ ሆስፒታል እንሂድ.. ሰውነቱን በእጇ ስትዳብሰው በጣም ያተኩሳል።
አይ ኡሚ እዚው ብሆን ይሻለኛል... አለመሄዱን ለማረጋገጥ አተኛኘቱን አመቻቸ።
ከትምህት ቤት ደውለው ነበር...አሞት ነው የቀረው ብያቸዋለው...
ሌላስ ምን አሉ?
ምንም...ሌላ ምን ይላሉ ልጄ?
አዲስ ተማሪ ገብቷል አላሉሽም? ሀሳቡ ሁሉ ሀዩ ጋር ስለሆነ እንጂ ከመች ጀምሮ ነው አዲስ ተማሪ ሲገባ ለወላጅ የሚነገረው። እናቱ በግርምት አፍጥጣ ስታየው ነው ምን እንዳላት ትዝ ያለው። ደነገጠ!
በቃ ኡሚ ልተኛ...ብተኛበት ይሻላል..አትጨነቂ አንቺ... ምንም እንዳትጠይቀው ፊቱን አዙሮ እንደሚተኛ ሰው አስመሰለ።

ሰው እንዴት አንድ ሰውን ለረጅም ጊዜ ከዛ ሰው ምንም አይነት የፍቅር ምላሽ ሳያገኝ ሊያፈቅር ይችላል? ያውም በዚ ጊዜ...ትናንት ተዋውቀው ዛሬ የሚጣሉ ሰዎች በበዙበት ዘመን.. ፍቅር ቃሉ ብቻ የቀረ በሚመስል ብዙዎቹ በፍቅር በሚቀልዱበት ዘመን...

ሀሰን እኮ የእውነት አፍቃሪ ነው። እሷን ያፈቀራት ገንዘብ አላት ብሎ ፣ ከሷ ጥቅምን ፈልጎ ወይም እሷ ትወደኛለች ብሎ አይደለም። በቃ ፍቅር የሚባለው ነገር በትክክል በልቡ ስለገባ ነው።
ሀሰን አሁንም ቢሆን ተስፋ አልቆረጠም። ስልኳ ካርድ ስለሌለው ይሆናል ወይም አልተመቻትም ይሆናል እያለ ዛሬም የሀዩን የስልክ ጥሪ እየጠበቀ ነው። ያልደወለችበትን መጥፎ ጎን ጭራሽ ማሰብ አልፈለገም።

*

ሀዩ አባታቸው ውስጥ ግቡ ብሏቸው ብትገባም ተረጋግታ ልትቀመጥ ግን አልቻለችም። ይሄን ያህል ስለምን ሊያወሩ ቢሆን ነው እንድንገባ ያደረጉን? በዛ ላይ ዛሬ ያለወትሮው የአባቷ ሙገሳ ፣ ፈገግታ ብቻ ብዙ ነገር ለየት ብሎባታል።
ልጆቹን ክፍል ካስገባች በኋላ ለሳሎኑ የምግብ መስሪያ ቤቱ ስለሚቀርብ እቃ እንደምታስቀምጥ መስላ ገብታ ጆሮዋን ወደሳሎኑ አስጠግታ ስለምን እንደሚያወሩ መስማት ጀመረች።

አባት፡ እቺት እንግዲ ...ቆንጆዋ የመጀመሪያ ልጄ ሀዩ ማለት እሷ ናት..

ሉቅማን፡ ማሻአላህ ቆንጅዬ ልጅ አለቾት...እና እሷስ ስለነገሩ ታውቃለች?

አባት፡ ኧረ አታውቅም... ዛሬ ጠዋት ነው እንደምትመጣ ብቻ የነገርኳቸው...ግን ልጄ አርቆ አሳቢ ናት...ቀድማ እንደምታስብ አልጠራጠርም...

አሁን ይባስ ለመስማማት ወደግድግዳው ተጠጋች። ስለምን እንደሚያወሩ ምንም ሊመጣላት አልቻለም።

ሉቅማን፡ ያው እንዳልኮት ነው...ካምፓስ እስከምትገባ ድረስ እዚው ሆና መማር ትችላለች...እኔ እሷን ጨምሮ ሁሉንም ልጆች አስተምራለሁ... ይሄ አመት አልቆ 12ተኛ ክፍልን ከጨረሰች በኋላ ግን ከእኔ ጋር እንድትኖር ነው የምፈልገው...

አባት፡ ኧረ ችግር የለውም...ሀያቴን እኔ አንድ ነገር ብያት እንቢ አትለኝም...በዛ ላይ የሚጠቅማትን በደንብ የምታውቅ ልጅ ናት...

አሁን ሁሉም ነገር ገባት። አባቷ ለሉቅማን ሊድራት እንደሆነ...በጣም ደነገጠች። ከወንድምና እህቶቿ ላለመነጠል ብላ ብዙ መስዋትነት ከፍላ ነበር እኮ። አሁንም ቢሆን እሷ ማግባት አትፈልግም።

ሉቅማን፡ እስከዛው ግን አደራዎትን እርሶ ሊጠብቋት ይገባል.. እስከነክብረንፅህናዋ ነው ላገባት የምፈልገው..

አባት፡ ኧረ ሀያቴ ወንድ ራሱ ጭራሽ አታውቅም እኮ...ለዚስ ጭራሽ አታስብ...

ሉቅማን፡ መርሀባ ያው ትምህርት ከተጀመረ ገና 1 ወር እንኳን ስላልሞላው ትምህርቷን አሁን መጀመር ትችላለች...

ሀዩ የምትገባበት ቀዳዳ ጠፋት። የምትይዝ የምትጨብጠውን አጣች። ለማታውቀና ለማትፈልገው ሰው ልትዳር ነው...መቀበል አትፈልግም።
በጭራሽ! በጭራሽ አላገባም! እልህ በተናነቀው የሲቃ ድምፅ ከሷ ውጪ ማንም በማይሰማ መልኩ ዝቅ አርጋ እየደጋገመች ተናገረች።
ያአላህ ስቃዬን አታብዛው...እኔ ደካማ ባርያህ ነኝ...ምንም ነገር ለመጋፈጥ አቅሙ የለኝም..ያ አላህ የልቤን አንተ ነህ የምታውቀው...በማልችለው ነገር አትፈትነኝ...እያለቀሰች እጇን ከፍ አርጋ ስሞታዋን ለአላህ አቀረበች።
ወይ ዱንያ ቀጣይስ ምን ይፈጠር ይሆን? አለች በልቧ ጭራሽ ያልጠበቀችው ነገር በመፈጠሩ ግራ እየተጋባች።

#ክፍል\ሰባት...⓻...ይቀጥላል
✿❯────「✿」─

BY የካምፓስ ህይወት_MAHIR


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Yecampas_Hiwet/6821

View MORE
Open in Telegram


የካምፓስ ህይወት_MAHIR Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Why Telegram?

Telegram has no known backdoors and, even though it is come in for criticism for using proprietary encryption methods instead of open-source ones, those have yet to be compromised. While no messaging app can guarantee a 100% impermeable defense against determined attackers, Telegram is vulnerabilities are few and either theoretical or based on spoof files fooling users into actively enabling an attack.

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

የካምፓስ ህይወት_MAHIR from us


Telegram የካምፓስ ህይወት_MAHIR
FROM USA