Notice: file_put_contents(): Write of 9893 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
Tikvah-University | Telegram Webview: TikvahUniversity/13750 -
Telegram Group & Telegram Channel
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የበንሳ ዳዬ ካምፓስ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ቅሬታ!

ባለፈው ሐሙስ ጥር 29/2017 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በንሳ ዳዬ ካምፓስ የተገኙ ተፈታኞች፥ "በካምፓሱ በተፈጠረ የኔትወርክ መቋረጥ ምክንያት" ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸውን ለቲክቫህ ተናግረዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን መውሰድ የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው የካምፓሱን አመራሮች ማነጋገራቸውን፣ ይሁን እንጂ ምንም አይነት መፍትሔ አለማግኘታቸውን ለቲክቫህ ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ኤክዚኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑትን ፍሬው ካሳ (ዶ/ር) ጠይቀናል፡፡

በተጠቀሰው ቀን የተሰጠውን የመውጫ ፈተና "በካምፓሱ ሦስት ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎች የሆኑ ዘጠኝ ተፈታኞች" አለመውሰዳቸውን ዋና ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል፡፡

በዕለቱ ፈተናው መሰጠት ሊጀምር ሲል የኢንተርኔት መቋረጥ መከሰቱንና ችግሩን በቶሎ በመቅረፍ ፈተናውን ለመስጠት ጥረት መደረጉን ፍሬው (ዶ/ር) አስረድተዋል፡፡

ካምፓሱ በሚገኝበት አካባቢ ባለ የመንገድ ሥራ ምክንያት የኢንተርኔት መቋረጥ ማጋጠሙን የገለፁት ኃላፊው፤ ከአካባቢው የኢትዮ ቴሌኮም ቅርንጫፍ ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት ጥረት ተደርጓል ብለዋል፡፡ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ጋር በመነጋገር ተፈታኞቹ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ጥረት መደረጉንም ገልፀዋል፡፡

የተማሪዎቹን ዕጣፈንታ በተመለከተ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ውይይት መደገሩንም አንስተዋል፡፡ በዚህም ያልተፈተኑት ተማሪዎች ዘጠኝ ብቻ በመሆናቸውና ለነሱ ብቻ ሌላ ፈተና ማዘጋጀት የሚቻል ባለመሆኑ፣ ተፈታኞቹ በቀጣይ ሰኔ ወር ላይ ፈተናቸውን እንዲወስዱ መግባባት ላይ መደረሱን ገልፀዋል፡፡ ውሳኔው ለተማሪዎቹ እንደተነገራቸውም ኃላፊው ለቲክቫህ ተናግረዋል፡፡

@tikvahuniversity



tg-me.com/TikvahUniversity/13750
Create:
Last Update:

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የበንሳ ዳዬ ካምፓስ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ቅሬታ!

ባለፈው ሐሙስ ጥር 29/2017 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በንሳ ዳዬ ካምፓስ የተገኙ ተፈታኞች፥ "በካምፓሱ በተፈጠረ የኔትወርክ መቋረጥ ምክንያት" ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸውን ለቲክቫህ ተናግረዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን መውሰድ የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው የካምፓሱን አመራሮች ማነጋገራቸውን፣ ይሁን እንጂ ምንም አይነት መፍትሔ አለማግኘታቸውን ለቲክቫህ ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ኤክዚኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑትን ፍሬው ካሳ (ዶ/ር) ጠይቀናል፡፡

በተጠቀሰው ቀን የተሰጠውን የመውጫ ፈተና "በካምፓሱ ሦስት ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎች የሆኑ ዘጠኝ ተፈታኞች" አለመውሰዳቸውን ዋና ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል፡፡

በዕለቱ ፈተናው መሰጠት ሊጀምር ሲል የኢንተርኔት መቋረጥ መከሰቱንና ችግሩን በቶሎ በመቅረፍ ፈተናውን ለመስጠት ጥረት መደረጉን ፍሬው (ዶ/ር) አስረድተዋል፡፡

ካምፓሱ በሚገኝበት አካባቢ ባለ የመንገድ ሥራ ምክንያት የኢንተርኔት መቋረጥ ማጋጠሙን የገለፁት ኃላፊው፤ ከአካባቢው የኢትዮ ቴሌኮም ቅርንጫፍ ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት ጥረት ተደርጓል ብለዋል፡፡ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ጋር በመነጋገር ተፈታኞቹ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ጥረት መደረጉንም ገልፀዋል፡፡

የተማሪዎቹን ዕጣፈንታ በተመለከተ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ውይይት መደገሩንም አንስተዋል፡፡ በዚህም ያልተፈተኑት ተማሪዎች ዘጠኝ ብቻ በመሆናቸውና ለነሱ ብቻ ሌላ ፈተና ማዘጋጀት የሚቻል ባለመሆኑ፣ ተፈታኞቹ በቀጣይ ሰኔ ወር ላይ ፈተናቸውን እንዲወስዱ መግባባት ላይ መደረሱን ገልፀዋል፡፡ ውሳኔው ለተማሪዎቹ እንደተነገራቸውም ኃላፊው ለቲክቫህ ተናግረዋል፡፡

@tikvahuniversity

BY Tikvah-University




Share with your friend now:
tg-me.com/TikvahUniversity/13750

View MORE
Open in Telegram


Tikvah University Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Newly uncovered hack campaign in Telegram

The campaign, which security firm Check Point has named Rampant Kitten, comprises two main components, one for Windows and the other for Android. Rampant Kitten’s objective is to steal Telegram messages, passwords, and two-factor authentication codes sent by SMS and then also take screenshots and record sounds within earshot of an infected phone, the researchers said in a post published on Friday.

Tikvah University from us


Telegram Tikvah-University
FROM USA