Telegram Group Search
#Gofa Disaster claims lives. Help is needed urgently. Condolences to the families affected by the tragedy.💔💔💔
Demeaning and Humiliating People will have dire Intergenerational Consequences.
===============
We have heard too many lies from #AbiyAhmed for us to be surprised by any he utters as a matter of routine. And we have heard him utter enough hate speech against--and vilification of--groups that he wants to exterminate. After all, he has now established his place as the Genocidaire-in-Chief of the 21st century.

But I never expected him--or anyone for that matter--to be so splendidly stupid as to say that the "Gurage people don't deserve their own State because they are dispersed and have no definite area they live in."

Nor have I expected him to tell the representatives of the Wolenee people that "the fact that they sit in the presence of the Prime Minister and asserting their identity (saying that they are Wolene) is in itself an achievement."

I think someone should tell him that enough is enough. Insulting and demeaning people only exacerbates problems, not solve them.
ሕዝብን በመሳደብና በማዋረድ ችግር አይፈታም!
===========
ሰሞኑን #አብይ_አህመድ፣ የጉራጌ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄን ለመመለስ እንዳንችል ያደረገን፣ "ጉራጌ ተበታትኖ የሚኖር መሆኑ ነው። አዲስ አበባ ውስጥ ነው ክልል የምንሰጠው? ወይስ ኦሮሚያ ውስጥ ነው? ወይስ የት ነው?" ማለቱን በመገናኛ ብዙሃን ለይ ተከታተልን።

ይሄን ባለበት በዚሁ መድረክ ላይ ስለ ወለኔ ሕዝብም፣ ከፓርቲው ተወካዮች ጥያቄ ቀርቦለት፣ እንዲህ ሲል አደመጥን፦
"እርስዎ ጠቅላይ ሚኒሥትር ጽ/ቤት ተገኝተው፣ 'እኔ ወለኔ ነኝ' ብለው መናገር መቻሎ እራሱ ትልቅ ድል መሆኑን መቀበል ይኖርብዎታል።" (ጥቅሱ ቃል በቃል አይደለም።)

አብይ፣ ክልልነት፣ መብት መሆኑን የማይረዳና ሊረዳና ሊቀበልም የማይፈልግ መሆኑ ግልፅ ነው። ክልልነት፣ እሱ በበጎ ፈቃዱ፣ እንደ ችሮታ፣ ለፈለገው የሚሰጠው፣ ላልፈለገው የሚነሳው ስጦታ እንደሆነ የሚያስብ መሆኑንም፣ ከዚህ በፊት ከሚናገራቸው ነገሮች ተነስተን መገመት አይከብድም። (በአብይ ዓለም፣ ችሮታና ጉቦ እንጂ መብትና ግዴታ አይታወቁምና።)

እንደ አንድ ብሔር የማንነት እውቅና ተሰጥቶት፣ በግልፅ በሕግና በተጨባጭ በሚታወቅ አካባቢ፣ የዞን አስተዳደር መሥርቶ (ከሞላ ጎደል) እራሱን ሲያስተዳድር የነበረን ሕዝብ፣ በዚህ ደረጃ፣ "ተበታትኖ የሚኖር ከመሆኑ የተነሳ" አድራሻው የማይታወቅ ነው ብሎ ማሳነስና ማበሻቀጥ ግን ሕዝቡን መስደብና ማዋረድ ነው።

ይሄ ችግርን አይፈታም። ይልቁንም፣ ችግሩን አወሳስቦ ለትውልዶች የሚተላለፍ ውጥረት ያነግሳል እንጂ።

ይሄ ንቀት ብቻ ሳይሆን የጥላቻ ንግግር ነው። ይሄ፣ ውሎ አድሮ ሕዝብን ለከፋ ጥቃት የሚያጋልጥ ጠንቀኛ ንግግር ነው።

ንግግሩ መታረም አለበት፤ መንግሥት ሕዝቡን ይቅርታ መጠየቅ አለበት።

በተመሳሳይ መልኩ፣ ለወለኔው ተወካይ፣ "እኔን በወለኔነት ማናገርዎ ትልቅ ድልና ዓይነተኛ ስኬት ነው" ብሎ የሕዝቡን የማንነትና የአካባቢ የራስ አስተዳደር ጥያቄ በዚህ ልክ ማሳነስ፣ ታላቅ ስድብ ነው። ንቀት ነው። ማንአለብኝነት ነው። መመፃደቅ ነው። በእኔ-አውቅልሃለሁ ስሜት ሌላውን አኮስሶ መመልከት (patronizing) ነው።

እንዲህ ያለ ንግግርና ተግባር ትውልዱን ምሬት ውስጥ በመጨመር፣ ወደ ማይፈለግ የኃይል እርምጃ እንዲገባ ያስገድዳል። ይሄም ፖለቲካውን (ኢትዮጵያ ውስጥ፣ ፖለቲካ ኖሮም አያውቅ እንጂ) ወደ ብረት እንዲገባ በማድረግ ማሕበረሰባዊ ጦረኝነትን (social militarizationን) ያስፋፋል።

ከዚህም አልፎ፣ አሁን በጥላቻ ቃል የተጀመረውን ንግግራዊ የኅይል ጥቃት (discursive violence) ወደ ለየለት ብሔር-ተኮር ጥቃት (እና ወደ ዘር ማጽዳትና ዘር ማጥፋት ዘመቻዎች) ያሸጋግረዋል።

ለነገሩ፣ ይብላኝለት ለሕዝቡ እንጂ፣ እንደ #አብይ_አህመድ ካለ የክፍለ-ዘመኑ አውራ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጻሚ መራሔ-መንግሥት፣ ከዚህ ሌላ ምን ይጠበቃል?

#AbiyAhmed_is_a_genocidaire!
#No_to_hate_speech!
#No_to_discursive_violence.
#Apologies_are_due_to_Gurage_and_Wolene_People!
ፌደሬሽንን መሻር፣ ጦርነትና ዕልቂት ያመጣል እንጂ መፍትሔ አይሆንም፦ ታሪክም የሚያስረዳው ይሄንኑ ሃቅ ነው።
=================
በ1962 (እኤአ): ኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ ጋር የነበራትን የፌዴሬሽን ውል ሽራ፣ ኤርትራን በጉልበት 'አዋሃድኩ' ያለች ዕለት፣ የኤርትራ ኃይሎች፣ የትጥቅ ትግል ለመጀመር የመጀመርያውን ጥይት ተኮሱ። በዚህ ቀን፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጀምሮ በኢምፓየሩ ውስጥ ሰፍኖ የነበረው አንፃራዊ ሰላም ደግሞ ላይጠራ ደፈረሰ። ከዚህ ቀን ጀምሮ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ በይፋ፣ በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ የሚነጋገሩበት የብረት ፖለቲካ ሆነ። የፖለቲካ ድልም፣ በደም የሚበየን ሆነ።

ገና በወጉ ያልተተገበረውን ፌደሬሽን በማፍረስ "አንድነትን አመጣን" ያሉት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የኢትዮጵያን የቁልቁለት ጉዞ አስጀመሩ። ለመቶ ሺህዎች እልቂት ምክንያት የሆነውን የጦርነት ወላፈን ለመመገብ፣ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን ወጣቶች መማገድ ጀመሩ።

በ2018ም (እኤአ)፣ ገና በወጉ ያልተተገበረውን የኢትዮጵያ ሕብረ-ብሔራዊ ፌደራሊዝም ለመሻር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በመንቀሳቀስ፣ እስከዚያ ወቅት ድረስ የነበረውን አንጻራዊ ሰላም በማናጋት፣ የዘር ማጥፋት ጦርነቶችን ለማድረግ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ጀመረ፣ አስጀመረ። "የአንድነት ጠበቃ ነን" የሚሉት የኢትዮ-አማራ ልሂቃንም" የዚህ ዘመቻ ፊታውራሪ በመሆን "ከመንግሥት ጎን ነን" እያሉ ፎከሩ። #አብይአህመድ ሥር ተኮልኩለው፣ ያንን ያረጀ፣ የነተበና የከሸፈ "የኣሃዳዊነት" ወግ፣ "መደመር" በሚል ካባ ሸፋፍነው፣ ፌደራሊዝሙንና ሕገ-መንግሥቱን ለመሻር፣ "የብሔር" ፖለቲካ የሚሉትን የብሔር-ተኮር ፍትህ ፖለቲካ (politics of ethno-national justice) ለማጥፋት፣ ለዚህም ሲባል "ብሔርተኞችን" (በመግደል) ለማጥፋት በሰፊው ተንቀሳቀሱ። የተነጣጠሩ የፖለቲካ ግድያዎችን፣ የጅምላ ፍጅትና እስርን፣ ማፈናቀልና የዘር-ማጽዳትን ፈጸሙ፣ አስፈጸሙ።

ይሄም አልበቃ ስላላቸው፣ ትግራይ ምርጫ ስላደረገ፣ "ሉዓላዊነታችን ተደፈረ፣ አንድነታችን አደጋ ተደቀነበት" እያሉ፣ የለየለት የዘር ማጥፋት ጦርነትን ለማድረግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር ጭምር ተባብረው፣ በትግራይ ሕዝብ ላይ ዘመቱ። የክፍለዘመኑን አውዳሚ ጦርነት ተገበሩ። በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብን ፈጁ።

ሕብረ-ብሔራዊ ፌደራሊዝምን በመሻር "አንድነትን ለማምጣት" በሚል ሰበብ የመዘዙት ሰይፍ፣ የዘር ማጥፋት ጦርነትን፣ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ቋንቋ ቋሚ አካል አደረጉ።

በመሆኑም፣ ዛሬም፣ አገሪቱ፣ በዘር ማጥፋት ጦርነቶች ማዕበል እየተናጠች ትገኛለች።

የሚገርመው፣ ባልጠበቁት መንገድ የዚህ ዓይነት ጦርነት ተጠቂ (ፈጻሚም) የሆኑት የኢትዮ-አማራ ልሂቃን፣ ዛሬም ከዚህ ጥፋት ለመታረም አለመቻላቸውና ዛሬም "የብሔር ፖለቲካን" እና ፌደራሊዝምን ማፍረስ፣ ቁልፍና ዋነኝ የፖለቲካ ማታገያ የትግል ርዕሰ-ገዳይ አድርገው መቀጠላቸው ነው።

ከዙህ በፊት ደጋግመን እንደተናገርነው፣ አንዴ የፌደራሊዝም ጎማዎች መሽከርከር ከጀመሩ በኋላ፣ ጎማውን ለማስቆም መሞከር፣ ሞካሪውን ጭዳ (cidhaa) ያደርጋል እንጂ መሽከርከሩን አያስቆመውም። Once the wheels of federalism have started to run, you may try to stop them at your own peril.

ሕብረ-ብሔራዊ ፌደራሊዝምን ለመሻር የተደረገው የቅርብ ዓመ ሙከራ፣ የመጨረሻ ውጤቱ፣ በሕብረ-ብሔራዊ ፌደሬሽን አማካኝነት ለመፍጠር የተሞከረውን ሕብረ-ብሔራዊ ትብብር፣ አጋርነት፣ እና ከብሔር ነፃ የሆነ (ethno-nationally secular) ወይም ሕብራዊ (plurinational) የሆነ ኢትዮጵያዊነት ድምጥማጡን አጥፍቶታል። የዘር ማጥፋት ጦርነትና የአገር ውድመት አስከትሏል።

ከዚህ አልፎም፣ ኢትዮጵያ ሊኖራት የሚችለውን በሆነ ዓይነት መዋቅር (በፌደሬሽን፣ በኮንፌደሬሽን፣ ወዘተ) የመሰባሰብና የትብብር ተስፋ ለዘላለሙ አክስሟል። በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ የነበረ (ኖሮ የሚያውቅ ከነበረ) የኢትዮጵያዊነት ተስፋን ገድሎአል። መልሶ እንዳያንሰራራ አድርጎ ቀብሮታል።

Adios!
#AbiyAhned's decision to effect currency floating may be the last straw.... Sad day for Ethiopia's poor.
ብድር ስለተፈቀድልን እንኳን ደስ አላችሁ!" አለ አሉ #አብይአህመድ!?!?! ኃፍረት አፍሮታልና: ባያፍር እንኳን ዝም አይልም? ወይ እነ ነውር-ጌጡ!
Channel photo updated
2024/08/03 08:21:46
Back to Top
HTML Embed Code: