Telegram Group Search
ቁጥር አይደሉም። ሁሉም የራሳቸው ህይወት፣ ህልሞችና ወዳጆች ነበሯቸው።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
“እና ከሁሉም ውድቀት በኋላ…  እጣፈንታችን  ህልማችንን  እንደማይመስል እንረዳለን።”
ደርዊሽ

@fuadkheyr
@fuadkheyr
"አትርገሙት… እርሱኮ አላህና መልዕከተኛውን ያፈቅራል።" ረሱል
በየጊዜው መጠጥ እየጠጣ የሚገረፍ ሰሓባቸውን አስመልክቶ የተናገሩት ቃል ነበር… ታውቃለህ? ጊዜ ያዳልጣል ፣ ትናንትና ዛሬ አንድ ላትሆን ትችላለህ… ስሜትህ አሸንፎህ ኃጢያት ውስጥ ትዘፈቅ ይሆናል… ምናልባት ለመቁጠር የሚያዳግት ኃጢያት ውስጥ…  ግን የአላህና የመልዕክተኛው ፍቅር ከውስጥህ አይለይ… መውደድህን ቀጥል… አንድ እለት ፍቅር በተግባር ይገለጣል… ውዴታህ ስሜትህን ያሸንፋል…

@Fuadkheyr
@fuadkheyr
ውድድሩ ተጀምሮአል… ያነበባችሁትን በአሪፍ መልኩ አጋሩን።

መፅሃፍን  ለፌስቡክ ልጥፍ በሚመች አጭር  ይዘት ደግሞ የመፃፍ ውድድር ጀምረናል። ለመነሻ እንዲሆን ሰሞኑን ከታተመው የ ABX መፅሀፍ እንጀምራለን። "ሰባሐል ኸይር" እነሆ መፅሀፉን ሙሉ ለሙሉ ማንበብና መረዳት ግዴታ ነው። የመፅሃፉን ሀሳብ አሳጥሮ  የተሻለ የፃፈ ይሸለማል።

ሽልማቱ ምንድነው? 
1ኛ ለወጣ ሰው 3000 ብር
2ኛ ለወጣ 1500 ብር
3ኛ ለወጣ ደግሞ 1000 ብር
ከ4 እስከ 10 ደግሞ የተሻለ ለፃፉት ለጥሩ ተሳትፎ 200 ብር።
በተጨማሪም ለአስሩም ተሸላሚዎች "አልሂጃብ" የተሰኘ  የመፅሃፍ ሽልማት ይኖራቸዋል። የኡማው ከንባብ መራቅ ያሳሰበው ወንድማችሁ ነው ይህንን ያቀረበው።  ተሳተፉ።  በዚህ የፌስቡክ አድራሻ ተሳተፉ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=938051771373055&id=100055047226745&mibextid=Nif5oz


@Fuadkheyr
@fuadkheyr
አንዳንድ ሰዎች አይንህን ብትሰጣቸው "ከነቅንድቡ አልሰጠንም" ብለው ያወራሉ።  እነዚህ ምንም ብታደርግላቸው መልካም ጎንህን ለመመልከት የሚከብዳቸው ሰዎች ናቸው።

@Fuadkheyr
@fuadkheyr
እና ከሁሉ ነገር በኋላ… ዱዓ የሌለበት ዓለም ከንቱ እንደሆነ ይገባሃል። በመጨረሻ… ስኬትም ስክነትም እዚህ መተናነስ ውስጥ እንደነበረ ትረዳለህ። አልሏሁመ!!

@fuadkheyr
@fuadkheyr
ድንገት አልነበረም። የቀደር መስመር ላይ ነው የተገናኛችሁት። በህይወትህ ላይ የሆኑ ትምህርቶችን ሰጥተውህ ያለፉት ሁሉ(ምናልባትም ክፉዎች)፣ ከዋክብቶች ሲሸሹህ ሰማይህን ሊያበሩልህ የመጡት ምርጥ ሰዎችህ ሁሉ… ለነርሱ የተወሰነላቸው የህይወት ዓለም ከተወሰነልህ የህይወት ዓለም ጋር እንዲነካካ ተፅፏል። ሌላ አይደለም።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
“ጌታዬ ሆይ! ባምፅህም እወድሃለሁ።”
ታላቁ ሰሓባ ዐምር ቢን ዓስ

@fuadkheyr
@fuadkheyr
"አንዲት ሴት ለቤተሰቦቿ ምግብ ማዘጋጀቷ  ፆመኞችን የማስፈጠር አጅር ውስጥ ይካተታል።"
ሸይኽ ኻሊድ መስለህ
@fuadkheyr
@fuadkheyr
ሰዎችም እድል ናቸው። በሆነ አጋጣሚ የምናገኛቸው ወይንም የምናጣቸው። ሁል ጊዜ በነበረበት የምናገኘው አይኖርም። ምናልባት ዛሬ ለኛ የተገባ ሰው… ነገ ላይሆን ይችላል።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
በዙሪያህ ያለውን ሁሉንም ነገር ለመረዳት አትሞክር። አንዳንድ ጉዳዮችን አለመረዳት ነው የሚሻለው። አንዳንዴ ነገሩን በመረዳትህ የሚመጣብህ የልቦና ቀውስና አንደበትህ ላይ የሰዎች ስም መመላለስ ብቻ ነው። …  በቃ ምናገባኝ ማለት አስፈላጊ ነው። በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ!

@fuadkheyr
@fuadkheyr
አቡበከር የቢላልን ያህል ድብደባ አላስተናገደም።  ድህነትም እንደአቡዘር አልፈተነችውም። ሰይፎች የኻሊድን ያህል ታዘውት በካሃዲያን አንገት ላይ አላሳረፈም። ግን  ከሁሉም የሚበልጥ ሰሓባ ነበር። ለነብዩ ልቡን ሰጥቷል። እንዳሻዎት ያድርጉኝ ብሏል። የልብ ሰው!!

@fuadkheyr
@fuadkheyr
ውስብስብ ጉዳዮቹን ለአላህ አደራ የሰጠ ሰው አይከስርም፣ አይፀፀትም።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
ግብፃዊው ፀሓፊና ፈላስፋ አኒስ መንሱር “የሰዎችን ውስጣዊ ዓለም እንዴት ነው ማወቅ የምንችለው?" የሚል ጥያቄ ተጠይቆ ነበር። እንዲህ ሲል መለሰ፦
“ባል ሚስቱ በታመመች ጊዜ ይታወቃል። ሚስት ደግሞ ባሏ በደኸየ ጊዜ ትታወቃለች። በመከራ(ችግር) ወቅት የእውነት ጓደኛ ይበጠራል። ልጆች ወላጆቻቸው ሲሸመግሉ ይታወቃሉ። ወንድምና እህቶች የውርስ ጊዜ ይታወቃሉ። ዘመድአዝማድ በብቸኝነት ውስጥ እንግዳ ሆነህ ሲያገኙህ ታውቃቸዋለህ። የእውነት ፍቅር ደግሞ ጥቅም ሲያበቃ ይታወቃል። አማኝ በፈተና ወቅት ይለያል።”

@fuadkheyr
@fuadkheyr
በጣም መንገብገብ፣ በጣም ክፍት መሆን፣ በጣም ራስን መስጠት ብዙ ጊዜ በጣም ያዋርዳል። ሁለተኛ ሰው ወይም አማራጭ የሚታይበት ሰው ያስደርጋል። ሁሉንም ነገር ሰጥቶ አንድ ነገር እንዲሰጡት የሚለምን አይነት ሰው ያስደርጋል። ሰዎች ያልተዘጋጁበትና ያላሰቡት ዓይነት ቦታ ስትመጣላቸው ይኮራሉ። በእጅ ያለወርቅ እንደመዳብ የሚሉትን ዓይነት እንዲሆኑ እናደርጋቸዋለን… በራሳችን እጅ። አንዳንዴ "አይመቸኝም" ያስፈልጋል። አንዳንዴ "ፈልገው ይደውሉ" ብሎ መተውም ያስፈልጋል። … ሲመስለኝ።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
አለመፍረድ። ትንሽ በእድሜ ከፍ ስንል፣ ትንሽ በሚፈትኑ የህይወት ተሞክሮዎች ስናልፍ፣ ትንሽ በኢማን መጨመርና መቀነስ ውስጥ ስንመላለስ… የምንረዳው እውነታ ነው። በቃ… "ምናልባት" ብለን ማሰብ እንድንችል የሚያደርገን የብስለት ደረጃ ነው።

በሆነ መልኩ ዱንያ ያንገላታቻቸውን ሰዎች ስታይ … "ገንዘብ እንዴት እንደሚሰራ ማያውቁ ሞኝ ድሆች" ብለህ ጭራሽ እንዳታስብ። ጭራሽ። ትዳር ዓለም ያልዘለቀላቸውን ሰዎች ስታይ "የባህሪ ደካሞች፣ ጥሬዎች" ብለህ እንዳትፈርድ። እነርሱ ብቻ የሚያውቁት ብዙ ማታውቀው ነገር አለ። "ምናልባት" የሚያስብልህ።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
የተሸፈነ ነገር አይገለጥም። በተለይ አንድ ባርያ በርሱና በጌታው መካከል ስላጠፋው ጥፋት ለሰዎች እንዲታያቸው የምንገልጠው መጋረጃ አይኖርም። ደብቀንለት ለመምከር ካልሆነ በቀር ጌታው ጋር ይጨርስ ዘንድ መተው የደጋጎች መገለጫ ነው። ሁሉም ሰው ከራሱ ጋር እንኳን የሚተፋፈርበት መጥፎ ጎን ይኖረዋል። ለራሳችን እንኳን ደግመን ለመንገር የሚቀፈን ስንት ኃጥያት አለን? በቃ ሰዎች አክብረውን እንኳ ጥሩ ጎናቸውን ካሳዩን ይበቃናል። የጥፋት መዝገባቸውን ሙሉ ለሙሉ ብናውቅ እንኳን ከጌታቸው ዘንድ ያወሩ ዘንድ እድል እንሰጣለን እንጂ ለሰው ምላስ አሳልፈን አንሰጥም። እየተሸፋፈንን የምንመካከርበት ሜዳ ናት… ዱንያ።

@fuadkheyr
@fuadkheyr
"ዱዓዬ እጣፈንታዬን ለመቀየር በቂ አልነበረም ማለት ነው?" የሚሉ ከርታታ ልቦች አሉ። በህይወት ልዩ መልኮች እንቅፋት የተመቱ ልቦች። በህመም፣ በእዳ፣ በትዳር አለመሳካት፣ በሁኔታዎች መዘበራረቅና ግራመጋባት የሚዋኙ ስሜቶችም እንዲሁ። ምን ያህል ጌትዬን ተለማምጠናል? … ከአለሙ ሁሉ እስኪያስቀድመን፣ ከጠያቂዎች ሁሉ እስኪመርጠን። እርሱ የሚለማመጡትን ይወዳል። የሚወደውን ደግሞ ይመርጣል።
@fuadkheyr
@fuadkheyr
ከጊዜ ጋር… የእድሜያችንን እኩሌታ ስናልፍ… ወደ አመሻሽ ላይ እንደድሮው ሁሉንም ነገራችንን ለሰው አንናገርም። መጥፎ የሆኑ ስሜቶቻችንን የመደበቅ ትልቅ ችሎታ ከወዴት እንደመጣ ሳናውቀው ይቆጣጠረናል። እንደጉድ እንችላለን። በጣም ከባድ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ምንም ያልሆንን ፅኑ መስሎ መታየት እንዴት እንደሆነ እንማራለን። አይገርምም? ወላጆቻችን የራሳቸውን ችግር ሲነግሩን እንኳን በአስተውሎት እናደምጣለን። የኛን ጉዳይ ሳንተነፍስላቸው። እንድናለቅስ የሚያስገድዱን ነገሮች ተፈጥረው እንኳን ፈገግታ ለመላበስ እንውተረተራለን። ፈገግታ የሚያሸነፈው የማይደረመስ የእንባ ግድብ ከየት መጣ? አቤት የአመሻሽ ውበት…

@fuadkheyr
@fuadkheyr
በመጨረሻም ዱንያ ከቤተሰብህ የበለጠ ውድ ነገር ልትሰጥህ አትችልም። ዱንያን በሙሉ ብትዞራት ከነርሱ የበለጠ ዋጋ ያለውን ነገር አታገኝም። ደስታን ከነርሱ ጋርና በነርሱ ውስጥ አብዝተህ ታሸተዋለህ፣ ትኖረዋለህ። ቤተሰብ ከዚያም ቤተሰብ ከዚያም ቤተሰብ።

@Fuadkheyr
@fuadkheyr
2024/07/17 07:04:13
Back to Top
HTML Embed Code: