Telegram Group Search
#23 💚💛❤️

ሰማዕተ ኢየሱስ የእውነት ምስክር
ህያው ነው በሰማይ ብፁዕ ነው በምድር ።

የኢትዮጵያ ገበዝ
የአራዳው ንጉስ
የልዳው ኮከብ
ሊቀ ሰማዕት
ፍጡነ ረድኤት
ፈረሰኛው ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቶቻችንን የረዳ ዛሬም ከኛ ጋር ነው ።

@ortodoxtewahedoo
#ሐምሌ 23

"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው።
ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደ እኔ ቅረብ።"

(መልክአ ጊዮርጊስ)

@ortodoxtewahedoo
Forwarded from ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈
​​👼 ቅዳሴ ማለት ምንም ማለት ነው?
🤔 በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
🥰 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት እነማን ይሆኑ?

😇 ካህናት በቅዳሴ ወቅት 2: 3: 4: 5: 7: 12: ወይም 24: ሆነው ከቀደሱ ምሳሌነቱ ምን ምን ይሆን?
🧎‍♂ እኛ ክርስቲያኖች ቅዳሴን ባስቀደስን ቁጥር 4 ነገሮች እናገኛለን ምን ይሆኑ?
👼 አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ እንዴት?


            ይ🀄️🀄️ሉ ይማሩ
                  👇🏾👇🏾👇🏾

https://www.tg-me.com/addlist/AQPOMxHXz_42NDE0
(የማቴዎስ ወንጌል 7 : 1-29)
----------
1-2፤ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።

3፤ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?

4፤ ወይም ወንድምህን። ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ።

5፤ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ።

6፤ በእግራቸው እንዳይረግጡት ተመልሰውም እንዳይነክሱአችሁ፥ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።

7፤ ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።

8፤ የሚለምነው ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልገውም ያገኛል፥ መዝጊያንም ለሚያንኳኳ ይከፈትለታል።

9፤ ወይስ ከእናንተ፥ ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው?
----------
10፤ ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን?

11፤ እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው?

12፤ እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና።

13፤ በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤

14፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።

15፤ የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።

16፤ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?

17፤ እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል።

18፤ መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት፥ ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም።
----------
19፤ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።

20፤ ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ።

21፤ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።

22፤ በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።

23፤ የዚያን ጊዜም። ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።

24፤ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል።

25፤ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም።

26፤ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል።

27፤ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ።
----------
28፤ ኢየሱስም ይህን ነገር በጨረሰ ጊዜ ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ፤ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን

29፤ እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና።

#መልካም ቀን

@ortodoxtewahedoo
ሐምሌ 26 በዚህች ዕለት መልካም ሽምግልና የነበረው የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጠባቂዋ ድካሟን ለመሳተፍ ክብር ይግባውና ለጌታችንም አሳዳጊው ለመሆኑ የተገባው #ጻድቁ_ዮሴፍ አረፈ። በአረፈበትም ጊዜ ጌታችን ወደ እርሱ መጥቶ እጆቹን በላዩ ላይ ጫነ ለሥጋውም መፍረስና መበስበስ እንዳያገኘው ኃይልን ሰጠው በአባቱ በያዕቆብም መቃብር አኖሩት።
(መጽሐፈ ስንክሳር)
በረከቱ ይደርብን!

@ortodoxtewahedoo
Audio
እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር ይኑራችሁ
        
Size:-26.4MB
Length:-1:15:56

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedoo
Audio
"እመቤታችን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር" ምን ማለት ነው??

መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረ ኪዳን
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ(ዶ.ር)
መጋቤ ብሉይ ዮሴፍ ደሳለኝ

@ortodoxtewahedoo
።።።።።።።።።። + ሐምሌ 26 + ።።።።።።።።።።
አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን

ደብረ መድኃኒት አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አንድነት ገዳም!
በዚኽች ዕለት ሐምሌ 26 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ታስበው የሚውሉት ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ ነው:-

‹‹ምንም ሳያስታጉል በየቀኑ ዕጣን የሚያሳርግ ወደ እግዚአብሔር መጸለይን የሚያበዛ ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ቤተ ክርስቲያን የሚላላክ አንድ መነኩሴ ነበር፡፡ ከዕለታትም በአንዲት ቀን እንቅልፍ መጥቶበት ተኝቶ ሳለ በዚያች ዕለት ሕልመ ሌሊት አገኘው፡፡ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ሕልመ ሌሊት እንዳገኘው አይቶ ስለ አቡነ ሰላማ ቤ/ክ ማዕጠንት መታጎል ታላቅ ኀዘን አዘነ፡፡ ያንጊዜም ሰይጣን ከሰይጣን ጋራ ‹‹…ወዳጄ ይህን መነኩሴ ዛሬ ጣልኩት፣ ከአገልግሎቱም አስታጎልኩት አየህን!›› እያለ ሲናገር ሰማው፡፡ ሌላኛውም ሰይጣን መልሶ ‹‹…ወዳጄ መልካም አድርገሃል፣ መጥጠተህ አፌን ሳመኝ›› አለውና ሁለቱም እርስ በእርሳቸው አፍ ለአፍ ሲሳሳሙ ያ መነኩሴ ይህን አይቶና ሰምቶ በመናደድ ድጋሚም በዚህ እንዳይፈተን በማሰብ ስለት ባለው ምላጭ አባለ ዘሩን ቆርጦ ጣለውና የብልቱን ቁራጭ ወደታላቅ ገደል ወረወረውና ለሰይጣን ‹‹ይህን እንካ እንደውሻ ቆጥሬልሃለሁና›› አለው፡፡

ሰይጣኑም ወዲያው በዱር አሞራ ተመስሎ የብልቱን ቁራጭ ጠልፎ ወሰደ፡፡ ነገር ግን የእግዚብሔር ሰው ድንቅ ተአምራትንም የሚያደርግ አባታችን ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ወዲያው ታላቅ የሆነ ነጭ ንስር መስሎ እየበረረ ሔዶ የመነኩሴውን የብልቱን ቁራጭ ከሰይጣን አፍ ቀምቶ ያንን ሰይጣን በሰይፍ ቆረጠውና ወደ አገልጋዩ መነኩሴ ቢሔድ ስለአገልግሎቱ መታጎል እያዘነ አገኘው፡፡ አባታችንም ‹‹…ወዳጄ አገልጋዬ ሆይ! እነሆ የሰውነትህን ብልት እንካ እንደቀድሞው ከሰውነትህ መልሼልሃሁ፤ እግዚአብሔር የፈጠረውን አካል ዳግመኛ አትቁረጥ፣ አስቀድሞም ከነበሩ በኋላም ከሚነሡ ይህንን ፈተና ታግሠው ካላላፉ ጽድቅ የለምና በቤተ ክርስቲያን ክህነትና ማዕረግ አይኖርህምና አካልህን አታጉድል፣ ሳትመረር ፈተናውን ታገሥ እንጂ፡፡ ያለመከራና ያለሥቃይ ጸጋ አትገኝምና…›› እያለ ከመከረው በኋላ ብፁዕና ቅዱስ ማር አቡነ ሰላማ ከመነኩሴው ተሰውሮ ዐረገ፡፡

ከዚህ በኋላ ያ መነኩሴ ፈጽሞ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ እስካረፈበት ዕለት ድረስ ጸሎትን አበዛ፡፡ በሞት ባረፈም ጊዜ በአባታችን ጸሎት መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ፡፡›› (ገድለ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገጽ 81-82)

አባታችን ባረፈ ጊዜ በዚህ አስደናቂ ገዳም ላይ ራሱ ጌታችን በአካል ለአባታችን ተገልጦላቸዋል፡፡ አባታችን ማር ሰላማም ቡሩካን በሆኑ እጆቹ ምድሪቱን እንደመሶብ አንሥቶ በሥሉስ ቅዱስ መንበር ፊት አቅርቦ አስባርኳታል፡፡ የገዳሙ አቀማመጥ እጅግ አስገራሚ ነው-ልክ እንደ ግሸን መስቀለኛ ቅርጽ ያለው ሲሆን በአራቱም አቅጣጫ የተለያዩ ምሥጢራት አሉት፡፡ በገዳሙ ምዕራባዊ ክፍል አስደናቂው ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ፣ በስተምሥራቅ የጻድቁ ቅዱስ መካነ መቃብር፣ በስተደቡብ መግቢያ በሩ፣ በስተሰሜን ጻድቁ ከዐለት ላይ ያፈለቋቸው ፈዋሽ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡

ለማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከሰማይ የወረደላቸው የእጅ መስቀላቸውና ቅዱስ መካነ መቃብራቸው በዚሁ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ታላቅ ጻዲቅ፣ መናኝ፣ ሐዋርያ፣ ጳጳስ....የሆነው ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በድፍን ኢትዮጵያ በአራቱ አቅጣጫ እየዞረ በተአምራቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ ሙታንን እያስነሣ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ እያጠመቀ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እየሠራና አገልጋይ የሚሆኑ ቀሳውስትን እየሾመ በሀገራችን ላይ ብርሃንን የፈነጠቀ ለኢትዮጵያ መግለጽ ከሚቻለው በላይ ታላቅ ባለውለታዋ ነው፡፡ ከአቡነ ሰላማ በፊት እኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ አልነበረንም፡፡ በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናትም ፈጽሞ አልነበሩንም፡፡ ይህን ሁሉ ያገኘነው በማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ሲታሰብ ከአባ ሰላማ ውለታ አንጻርና እንደሠራላት እጅግ ታላቅ ሥራ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቁን እንደሚገባው መጠን አላከበረችውም ማለት ይቻላል፡፡ ጌታችንም በመጨረሻ ቃልኪዳን ሲሰጠው ‹‹ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት ከፍ ያሉ ክብራትንና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሁህ›› ነው ያለው፡፡

የማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

(ጽሑፍ ከ ገድላት አንደበት ገጽ የተወሰደ
ሥዕለ ቅዱስ በሠዓሊ ዘሪሁን ገ/ወልድ

@ortodoxtewahedoo
#መድኃኔዓለም

" ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው ፣
ይህን ያህል ትዕግስት እንደ ምን ያለ ትዕግስት ነው ፣
ይህን ያህል ዝምታ እንደ ምን ያለ ዝምታ ነው ፣
ይህን ያህል ቸርነት እንደ ምን ያለ ቸርነት ነው ፣
ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደ ምን ያለ ፍቅር ነው "

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በቅዳሴው ።

@ortodoxtewahedoo
Audio
ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው
        
Size:-13.8MB
Length:-39:45

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedoo
2024/08/06 01:49:08
Back to Top
HTML Embed Code: