Telegram Group Search
#AMAZON_FASHION

የወንድ አልባሳትና ጫማ አስመጪ ኖት ? export standard አልባሳትና ጫማ አሎት ፤ አማዞን ፋሽን ይረከቦታል።

ሱቅ መክፈት አስበው የሱቅ ኪራይ  አሳስቦታል ? ከአማዞን ፋሽን ጋ አብረው ይስሩ ሱቅም ከፉተዉ አላዋጣ ካሎት ወይም በኦንላይን እየሰሩ ከሆነ ከአማዞን ጋር በመስራት ተደራሽነቶን ያስፉ።
ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ።  ለበለጠ መረጃና ለመመዝገብ   @fuaib ወይም 0911072936 ይደዉሉ
#Amhara

ከሰሞኑን በአማራ ክልል፣ በባህርዳር ከተማ የተለያዩ የመንግሥት አካላት ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ከተካሄደ የሰላም ኮንፈረንስ በኃሏ ተቋቁሟል የተባለው ' አመቻች የሰላም ምክር ቤት ' በአማራ ክልል እየተደረገ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ነው ብሏል።

ምክር ቤቱ በዚህ ጦርነት ፥ " ወንድም ከወንድሙ፣ ልጅም ከአባቱ ጋር ነው እየተገዳደለ ያለው " ሲል ገልጿል።

ለፌዴራል መንግሥት / ለአማራ ክልላዊ መንግሥት እና ለፋኖ ኃይሎች ሲል በስም ጠርቶ ባቀረበው የሰላም ጥሪ " የወገናችሁን ስቃይ ተረድታችሁ ምንም መሸናነፍ በማትችሉት ጦርነት ከመቆየት ሁለታችሁም ማሸነፍ ወደምትችሉት ንግግር እና ድርድር እንድትመጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ም/ ቤቱ መንግሥት እና የፋኖ ኃይሎች ወደ ሰላም መድረክ እንዲመጡ ለማመቻቸት እንደሚሰራ አመልክቷል።

" በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ንጹሃን ይገደላሉ፣ በጠራራ ጸሃይ ያለ ከልካይ ይዘረፋሉ  " ያለው ምክር ቤቱ ከ12 እስከ 13 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን አመልክቷል።

መንግሥት ጦርነቱን በድርድር ለመቋጨት ፍቃደኛ እንደሆነ ገልጾ " ብዙ መሪ እና አደረጃጀት ያላቸው የፋኖ ታጣቂዎች ለመደራደር ወደ አንድ መምጣት አለባቸው በማለቱ ይህ የሰላምና ድርድር አመቻች ምክር ቤት መቋቋሙ ተነግሯል።

ምክር ቤቱ 15 አባላት ያሉት ነው።

በሌላ በኩል ፥ ከሰሞኑን በርካታ ሰዎች በክልሉ መገደላቸው ተሰምቷል።

በሰሜን ጎንደር ዞን ፤ በዳባት ወረዳ፣ በመንግስት የጸጥታ አካላት እና ፋኖ ኃይሎች መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የፓሊስ አባላት መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ሁነቱን በቅርበት ሲከታተሉ የነበሩ ነዋሪ ፤ " ከተማው ውስጥ አሁንም ሀዘን/ልቅሶ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ሀዘኑ የተፈጠረው በአካባቢው ላይ ከ ‘ ፋኖ ’ ጋር በነበረ ውጊያ በርካታ የአካባቢው የጸጥታ አባላት ስለተገደሉ መሆኑን አረጋግጫለሁ " ብለዋል።

የሟቾች ቁጥር ምን ያህል ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ " የሟቾች ቁጥር ከ115 በላይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሟቾቹን በተመለከተም አድማ ብተና ሚሊሻና ፖሊስ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ሌሎች ነዋሪዎች የሟቾች ቁጥር እስከ 130 እንደሚደርስ ንጹሐን እንደቆሰሉ ገልጸው ሰሞኑን ከተማዋ ከባድ ሀዘን እንዳስተናገደች ተናግረዋል።

ስለግድያው ምላሽ የጠየቅነው የዳባት ወረዳ ከንቲባ ጽ/ቤት፣ ጉዳዩን በጽሞና ከሰማ በኋላ ማብራሪያ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም።

በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ባአዊ ዞን የቲሊሊ ወረዳ ነዋሪዎች ደግሞ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች 3 ሰዎችን ከቲሊሊ ሆቴል አውጥተው ገድለዋል ሲሉ ከሰዋል።

ሌሎች 2 ሰዎችም ተገድለዋል። በድምሩ 5 ንጹሐን በቲሊሊ ወረዳ መገደላቸውን ተናግተዋል።

በቦታው የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነበር እንዴ ? በሚል ለነዋሪዎቹ ለቀረበው ጥያቄ ምንም ተኩስ እንዳልነበር፣ ግማሾቹን መንገድ ላይ በሚጓዙበት፣ ሌሎቹን ደግሞ ከሆቴል አስወጥተው እንደገሏቸው አስረድተዋል።

የመንግስት አካላት ስለሁኔታው እንዲያብራሩልን ብንጠይቅም ፍቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ ባለፈም ፥ በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ  " ሾላ  ሜዳ " በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና 4 የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ አማርኛው ዘግቧል።

በጥቃቱት ከአያቶቹ ጋር የሚኖር የ14 ዓመት ታዳጊ መገደሉን ፥ አንድ የአይን እማኝ ደግሞ አንድ ሻይ ቤት 11 ሰዎች መገደላቸውን በ20ዎቹ እድሜ የሚገኝ ወንድማቸው ተገድሎ ሜዳ ላይ እንዳገኙት ተናግረዋል።

ሌላ የአይን እማኝ የ11ዱ ሟቾችን ስም ዝርዝር መሰብሰብ እንደቻሉ ሰኔ 20 ቀን/2016 ዓ/ም 4 ተጨማሪ አስከሬን እንደተገኘ ገልጸዋል።

የጸጥታ ኃይሎቹ በአካባቢው ለለቅሶ መጥተዋል የተባሉ 3 የፋኖ ታጣቂዎችን ተከትለው ሳይመጡ እንዳልቀረና ስለ ታጣቂዎቹ መረጃ በመፈለግ ግድያውን እንደተፈጸመ አክለዋል።

በተመሳሳይ በሰሜን ጎጃም ዞን ፤ በይልማና ዴንሳ ወረዳ አዴት ከተማ ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 11 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፥ በእለቱ የፋኖ ታጣቂዎች እና የመንግሥት ኃይሎች ለሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ይህን ተከትሎ ጥቃቱ መፈጸሙን አንድ ሴትና 10 ወንዶች እንደተገደሉ ገልጸዋል።

ግድያው የ ' ፋኖ ታጣቂዎች ' ከተማይቱን ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ 02 ቀበሌ እርሻ ሰብል በተባለ ሰፈር መንገድ ላይ እና ቤት ለቤት መፈጸሙን ገልጸዋል።

" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " በሚል ግድያው ተፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።

ፋኖ በከተማው ተቆጣጥሮ ውሎ በወጣበት ሰዓት የመንግስት ጸጥታ ኃይል ተመቶ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በተፈጠረው ክስተት ከተማዋ በከባድ ሀዘን ውስጥ መውደቋን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል ፤ ያለው ጦርነት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በተለያየ ቦታ እየተፈጠረ ባለው ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው።

ከሰሞኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ህዝቡ በሰላም እጦት የከፋ ችግር ላይ ወድቆ እንደሚገኝ ተናግረው ፥ መገዳደሉና ፣ በጠላትነት መፈላለጉ እንዲያበቃ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አገኘሁ ተሻገር፥ " በቃ! እስኪበቃን ተገዳድለናል ፣ እስኪበቃን ተዋጋን ስለዚህ አሁን ላይ ይብቃን ፣ መፍትሔው ንግግር ነው ፣ መነጋገር ነው ፣ መከባበር ነው " ሲሉ ነበር የተናገሩት።

#Ethiopia
#AmharaRegion

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በራሳቸው የዘጉ ተቋማት ዝርዝር.pdf
" ትምህርት ቤታችን አልተዘጋም " - ፕራይም ብሪጅ

ፕራይም ብሪጅ ትምህርት ቤት እንዳልተዘጋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳወቀ።

ከሰሞኑን የአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በከተማይቱ በራሳቸው የተዘጉ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይፋ አድርጎ ነበር።

ከዚህ ዝርዝር ውስጥ አንዱ ፕራም ብሪጅ ትምህርት ቤር ሲሆን ትምህርት ቤቱ ግን እንዳልተዘጋ ገልጿል።

ባለስልጣን መ/ቤቱም በጻፈው ደብዳቤ ኮልፌ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ ስር ከሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም የእውቅና ፈቃድ እድሳት ሰርተፊኬት ወስዶ በማስተማር ሃደት ላይ እንደነበር ገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ እና አዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ መልሶ ማደራጀት ቀድሞ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮልፌ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ የነበረው በአዲሱ አደረጃጀት በሸገር ከተማ መስተዳድር በፉሪ ክ/ከተማ በሙዳ ፉሪ ወረዳ ስር በመካለሉ በባለስልጣን መ/ቤቱ የነበረውን የእውቅና ፈቃድ ሰርተፊኬት መመለሱንም አመልክቷል።

ቀጥሎም በአዲሱ አደረጃጀት በሽገር ከተማ በፉሪ ክ/ከተማ በሙዳ ፊሪ ወረዳ ስር ፈቃድ ወስዶ በማስተማር ላይ መቀጠሉን አሳውቋል።

በት/ቤቱ ልጆቻቸውን የሚያስተምሩ ወላጆች እና ማህበረሰቡ ይህን እንዲረዱ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
#Tigray
 
ከቀናት በፊት በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ከተማ በጠራራ ፀሃይ በገበያ ቦታ በቢላዋ ዘግናኝ ግድያ ተፈጽሟል።

የግድያው መነሻ ቂም በቀል እንደሆነ ተነግሯል።

ግድያው መቼ ? እንዴት ? ለምን ተፈፀመ ?

ቀኑ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም ሲሆን ከቀኑ 11:00 ሰዓት ሰውና መኪና በብዛት በሚተላለፍበት በአስፓልት ላይ ነው ግድያው የተፈፀመው። 

የጭካኔ ግድያ የፈፀመው መምህር በየነ ገ/ማርያም የተባለ ግለሰብ ሲሆን ሟች ደግሞ ኣግደው ተስፋዓይኑ ይበላል።

ሟችና ገዳይ የስጋ ዘመዳሞች ሲሆኑ ሟች አግደው በ2013 ዓ.ም ታጣቂ ሚልሻ እያለ ከገዳይ መምህር በየነ ገ/ማርያም ታላቅ ወንድም ሆነው አልኮል ሲጠጡ እምሽተው በመካከላቸው በተፈጠረው ጊዚያዊ ጭቅጭቅ በመናደድ አግደው የመምህር በየነ ታላቅ ወንድም ደጋግሞ ተኩሶ በጭካኔ እንደገደለና በዚህም ቤተሰብ ክፉኛ ሀዘን ላይ ወድቆ ነበር።

በወንድሙ ላይ በተፈፀመው ግድያ ቂም የቋጠረው መምህር በየነ ገ/ማርያም በተራው ሰኔ 18/2016 ዓ.ም በቀን በጠራራ ፀሃይ ሰውና መኪና በብዛት በሚተላለፍበት አደባባይ በሰራው ወንጀል ታስሮ ከእስር ቤት የወጣውን አግደውን በቢላዋ ደጋግሞ በመውጋት እንደገደለው ተሰምቷል።

ለመሆኑ ግለሰቡ እንዴት ከእስር ወጣ ?

አሁን ግድያ የተፈፀመበት ግለሰብ ግድያ የፈፀመው ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ነው።

ያኔ በቁጥጥር ስር ውሎ ነበር። ቢሆንም ጦርነት ሲጀመር ፍርዱ ሳይጨርስ ከሌሎች እስረኞች ጋር በጋራ ከእስር ቤት ተለቀቀ።

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ ተመልሶ ወደ እስር ቤት አልተመለሰም። በዚሁ ሁኔታ እያለ ነው በቂም በቀል የተገደለው።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በ5ቱ ኮሪደር ልማት ስራ 16 ሺህ ሰዎች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ከተማ  ፦ ° መንገዶችን የማስፋት ፣ ° የመንገድ ዳሮችን የማሳመር ፣ ° የእግረኛና የሳይክል ብስክሌት መሄጃዎችን መስራት ° የቴሌ፣ የመብራት ኬብሎችን ወደ መሬት መቅበር ° የውሃ ፍሳሽ መሄጃዎችን መስራት ° ፕላዛዎችን መስራት የሚያጠቃልለው የኮሪደር ልማት ስራ በ5 ኮሪደሮች በመሰራት ላይ…
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ፤ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የክረምት ወቅቱ ሳይጠናከር ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ከተማው አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

እስካሁን ባለው የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር እንዲሁም ከሜክሲኮ እስከ ሳር ቤት ያለው ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተመርቋል።

ከዚህ ቀደም ፦
- ከ4 ኪሎ - ፒያሳና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ፣
- ከ4 ኪሎ አደባባይ በእንግሊዝ ኤምባሲ መገናኛ ፣
- ከሜክሲኮ ሳር ቤት በጎተራ ወሎ ሰፈር አደባባይ፣
- ከ4 ኪሎ መስቀል አደባባይ ቦሌ ድልድይ ፣
- ከቦሌ ድልድይ በመገናኛ እስከ አፍሪካ ኮንፌሽን አጠቃላይ 5 የኮሪደር ስራ እየተሰራ እንደሆነ መነገሩ ይታወሳል።

በከተማው እየተሰራ ያለው የኮሪደር ስራ ፥

ብዙሃን የሚጠቀሙበትን የእግረኞች መንገድ ማስፋት ምቹ ማድረግ፣
የተሽከርካሪ መንገዶችን ማስፋት፣ መታደስ ያለባቸውን የአስፋልት መንገዶች ማደስ፣
አላስፈላጊ ናቸው የተባሉ የመንገድ ማካፈያዎችን አንስቶ መንገድ ማስፋት፣
የመኪና ማቆሚያዎችን የመስራት፣
የመንገዶችን ዳር ማሳመር፣
የቴሌ፣ የመብራት ኬብሎችን ወደ መሬት መቅበር
ዘመናዊ የውሃ ፍሳሽ መሄጃዎችን መስራት
የሳይክል መንገድ መስራት
ፕላዛዎችን መስራት ሌሎች ተያያዥ ስራዎች የሚያጠቃልል ነው።

አብሮም ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃ ቤቶች እየተሰሩ ነው።

ሁሉንም የኮሪደር ስራዎች የክረምቱ ወቅት ሳይጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማ አስተዳደሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

እንደ ከተማ አስተዳደሩ መረጃ ስራዎች በሳምንት 7 ቀን ለ24 ሰዓት (ማታ እና ቀን) እየተሰሩ ይገኛሉ።

ከዚህ ቀደም በአጠቃላይ ከ16 ሺ በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው መገለጹ ይታወሳል።

በሌላ በኩል ፥ ህንጻዎችን የማደስ ፣ ወደ ንግድ / ቢዝነስ ማዕከልነት የመቀየር እና በስታንዳርድ የተቀመጠውን መስፈርት / የህንጻዎች ቀለም ጭምር) እንዲያሟሉ እየተደረገ ነው ተብሏል።

ሌላው ደግሞ የኮሪደር ልማት በሚከናወንባቸው አካባቢዎች እና በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚገኙ የንግድና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከተለመደው የሥራ ሠዓት በተጨማሪ ቢያንስ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰአት ድረስ ክፍት በማድረግ የንግድ እና የአገልግሎት ስራዎች እንዲካሄዱ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ወስኗል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃጫሉን ግድያ የፈጸሙትን ታውቃለችሁ አውጡልን " - ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ ትላንት በ " አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን " አዘጋጅነት የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተሰዋበት ዝክር እና የሃጫሉ አዋርድ ተካሂዷል። በዚሁ ዝግጅት ላይ የአርቲስት ሃጫሉ ባለቤትና የሃጫሉ ፋውንዴሽን ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፋንቱ ደምሴ ንግግር ያደረገች ሲሆን በንግግሯም ከባለቤቷ ግድያ ጋር በተያያዘ ዛሬም ድረስ ፍትሕ እንዳልተገኘ…
" ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ " - ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ

ትላንት አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተገደለበት 4ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 3ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች እውቅና አግኝተዋል፡፡

በዚሁ መድረክ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ባለቤት እና የሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን የበላይ ኃላፊ ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ ንግግር አድርገው ነበር።

ወ/ሮ ፋንቱ ፤ " ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የሃጫሉ ባለቤት አሁንም ድረስ ትልቁ መሻታቸው የግድያው እውነታ ከምንጩ እንዲመረመር መሆኑን አስረድተዋል፡፡

" አርቲስቱ የተገደለው ለፖለቲካ እቅድ ማስፈጸሚያ " መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

" ህዝብን ተስፋ እናስቆርጣለን ያሉ በራሳቸው ተስፋ ቆርጠው ሃጫሉን በሚሊዮኖች ልብ ውስጥ አኖሩት " በማለት ገልጸዋል።

" እውነት ተደብቋል " ያሉት ወ/ሮ ፋንቱ የአርቲስቱ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ መናገር እና መጠየቅ እንደማያቆሙም አስረድተዋል፡፡

" የምታውቁት እያላችሁ ምንም እንደማያውቁ አትሁኑ " ያሉት ወ/ሮ ፋንቱ መንግስትም ሆነ ከመንግስት ውጪ ያሉ ያሏቸው የአርቲስቱን እውነተኛ የአገዳደል ሚስጥር የሚያውቁ " እውነታው ወጥቶ " ፍትህ እንዲረጋገጥ ስሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" ገዳይና አስገዳዩን ለህግ አቅርቡልን " በማለትም ማንም በዚህ ንጽህናውን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል፡፡

አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ሰኔ 22 ቀን 2012  ዓ/ም አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ገላን ኮንዶሚኒየም ተብሎ በሚታወቅ አከባቢ ተገድሎ መገኘቱ ይታወሳል፡፡

ግድያውን ተከትሎም በማግስቱ በመላው ኦሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰው ከፍተኛ አመጽ የበርካታ ሰዎች ህይወት መጥፋቱና እጅግ የበዛ ንብረትም መውደም አይዘነጋም።

የአርቲስቱን ግድያ ተከትሎ ግድያው ላይ ተሳትፈዋል በተባሉት ሶስት ሰዎች ላይም አቃቤህግ ክስ መስርቶ በአንደኛው ተከሳሽ ላይ የእድሜ ልክ እስራት እና በሁለተኛው ላይ ደግሞ የ18 ዓመት ጽኑ እስራት ማበየኑ ይታወቃል፡፡

ነገር ግን የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ቤሰተቦች በዚህ የህግ ሂደቱ ብዙ እምነት እንደሌላቸውና " እውነተኛው ፍትህ " እንዲረጋገጥ እንደሚፈልጉ ደጋግመው ያነሳሉ፡፡

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ (DW) ነው።

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia

ክረምቱን ልጆችዎ በዲኤስቲቪ እየተዝናኑ ይማራሉ፣ ዓለምን እየጎበኙ ይመራመራሉ! 👩🏽‍🚀

በየትኛውም ዕድሜ ላሉ ልጆችዎ እንደ ኒክ ጁኒየር፥ ማይንድሴት፥ ኒኮሎዲየን እና ጂምጃም ያሉ ቻናሎችን በወር ከ350 ብር ጀምሮ በዲኤስቲቪ።

ክረምቱን ልጆችዎ በዲኤስቲቪ እየተዝናኑ ይማሩ!

የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇👇👇
https://bit.ly/3yBcOHc

#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
#Amhara

የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል ምን አለ ?

- ይህ የ ' ሰላም ካንውስል ' በአማራ ክልል ውስጥ የተፈጠረውን አለመስማማት እና አለመግባባት ተከትሎ የተከሰተውን የእርስ በእርስ ጦርነት በሰላም ለመቋጨት መንግሥትን እና ታጥቀው ጫካ የገቡ የፋኖ አባላትን ለማደራደርና ለማወያየት ይቻል ዘንድ ለመመቻቸት የተሰየመ ነው።

- ድርሻው መንግሥት እና የፋኖ አባላትን ለድርድር፣ ለውይይት እንዲበቁ ማመቻቸት ብቻ ነው።

- ያለ ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ደረጃ ፣ በየትኛውም ቦታ ፣ በየትኛውም አደራዳሪ የመንግሥት ኃይሎች እና በጫካ የሚገኙ የፋኖ ወንድሞቻችን ቢያስን ዘላቂ ተኩስ ለማቆም ንግግር እና ድርድር እንዲያደርጉ ይህ ካውንስል ተሰይሟል።

- በጦርነት እንጨራረሳለን እንጂ አንሸናነፍም።

- የአማራ ህዝብ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ ምስቅልቅል ውስጥ ይገኛል።

- ግጭቱ አጠቃላይ ሀገሪቱን ለከፍተኛ ጉዳት እና ወደባሰ የድህነት አረንቋ እየከተታት ይገኛል።

- ለዚህ ግጭት መነሻ የአማራ ህዝብ ለዘመናት ሲጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች በሰለጠነ ንግግር እና ድርድር አለመፈታታቸው ወይም ደግሞ የሚፈቱበትን ሂደት የሚያመለክት ግልጽ ፍኖተ ካርታ አለመቀመጡ ነው።

የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች ተብለው የተለዩት ፦
° የተዛባ ትርክት ማረቅና ማስተካከል
° ህገመንግስት ይሻሻልልን
° የወሰን እና ማንነት ጉዳይ
° ፍትሃዊ የኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ውክልና ጉዳይ
° በሌሎች ክልሎች የሚኖሩ የአማራ ህዝብ ጉዳይ
° የአዲስ አበባ የመልካም አስተዳደር እና አድሏዊ አሰራር ችግር አለመቀረፉ
° በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ንጹሃን የአማራ ተወላጆች ለሚደርስባቸው ግድያ እና መፈናቀል ተጠያቂነት አለማስፈን ጉዳይ .. የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

- እነዚህ ጥያቄዎች በቅንነት በሀገሪቱ ጥላ ስር በንግግር እና በድርድር ሊፈቱ የሚገባቸው እንጂ ወደ ጦርነት የሚያስገቡ አልነበሩም።

- የክልሉ መንግሥት በህዝብ ዘንድ ያለው ቅቡልነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሄዷል።

- ክልሉም ከችግሩ ሚያወጣው ፣ የተደራጀ የፖለቲካ እሳቤ የሚፈጥርለት ምሁር የመከነ እስከሚስል ደርሷል።

- ላለፉት ዓመታት የኢኮኖሚን ችግር የሚቀርፍ የማሻሻያ ድጋፍ ይደረጋል ሲባል በተለያዩ አጀንዳዎች በመወጠር እና የደህንነት ስጋት ውስጥ እንዲወቅ ሆኖ በከፋ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል ውስጥ ይገኛል።

- ከ ' ህወሓት ' ጋር የተደረገው ስምምነት በአግባቡ ሳይተገበርና የአማራ ህዝብ ህልውና ስጋት ዋስትና ሳይበጅለት ቀርቶ ነው የክልሉ የጸጥታ ችግር ተባብሶ ከ2015 ሀምሌ መጨረሻ አንስቶ በነፍጥ የታገዘ ግጭት የጀመረው። በዚህ ምክንያት ለአንድ አመት የሚጠጋ ጊዜ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነበር።

- ለአንድ አመት በተጠጋው ጦርነት የክልሉ ህዝብ መከራ እና ምስቅልቅል ህይወት ውስጥ ይገኛል።

- በአሁን ጊዜ በርካታ የክልሉ አካባቢዎች በመንግስት እና የአማራን ህዝብ ጥያቄ ለማስመለስ ጫካ ገብተናል ባሉ ' ፋኖዎች ' መካከል በሚካሄድ በትጥቅ የታገዘ ጦርነት ፦
ንጹሃን ተገድለዋል።
ከ12 እስከ 13 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል።
ከ3.6 ሚሊዮን በላይ ህጻናት ከትምህርት ገበታቸው ውጭ ሆነዋል።
የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ክፉኛ ተጎድቷል።
የግል እና የመንግስት ተቋማት ከቦታ ቦታ ለመጓጓዝ ባለመቻላቸው አገልግሎት አሰጣት ክፉኛ ተዛብቷል።
ነፍሰጡር እናቶች በአግባቡ የአምቡላንስ አገልግሎት አያገኙም።
እናቶች እና ህጻናትን ጨምሮ ከጦርነት ተሳትፎ ውጭ የሆኑ ዜጎች ለከፋ የስነልቦና ጫና ተዳርገዋል።
እጋታ ተስፋፍቷል።
ዜጎች ያለ ከልካያ በጠራራ ጸሀይ ይዘረፋሉ፤ ይገደላሉ።
ታላላቅ ፕሮጀክቶች ተስተጓጉለዋል።
ህዝቡ ለሁለት ወገን ግብርና ቀረጥ ይከፍላል።

ይህ ጦርነቱ ካመጣቸው መዘዞች መካከል ነው።

- ችግሩን ለመቅረፍ በአዲስ አበባ እና ከባህር ዳር ከህብረተሰቡ የተውጣጣ ክፍል ውይይት አድርጓል። በውይይቶቹ የሀገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች እና የሲቪል አመራሮችም ተገኝተው ነበር።

- ጦርነቱ አሸናፊነት የሌለው የእርስ በእርስ ጦርነት ስለሆነ በንግግር በውይይት በድርድር ይፈታ የሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል።

- በክልል ፣ በሀገር ደረጃ በየትኛውም መንገድ ይሁን የአማራን ህዝብ ጥቅም ይዤ ነው የምዋጋው ከሚል ኃይል ጋር ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ድርድር እንዲደረግ የመፍትሄ ሀሳብ ተቀምጧል።

- መንግሥት አሸናፊ የሌለው ይሄ አውዳሚ ጦርነት በንግግር እና ድርድር ለመፍታት " ፍቃደኛ ነኝ ነገር ግን ፋኖ አደረጃጀቱና መሪው ብዙ ነው ለመደራደር አንድ መሆን አለባቸው " በማለቱ የድርድሩ ደረጃ ጊዜ ፣ ቦታ እና ተደራዳሪዎች ተለይተው ለንግግር እና ድርድር እንዲበቁ ይህ 15 አባላት ያሉት የሰላም ካውንስል ተመርጧል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Tigray

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል።

ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው እንደነበር እና ቅዳሜ የማጓጓዝ ስራው መጀመሩ ተሰምቷል።

ወደ ቄያቸው እንደሚማለሱ የተነገራቸው ተፈናቃዮች ወደ 10 ሺህ እንደሚደርሱ ተነግሯል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምንጮች ሌሎችንም ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስና ወደ ቤታቸው የማስገባት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በምዕራባዊ ዞን በቀጣይ ሳምንታት እንደሚካሄድ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደመወዝ #ደቡብኢትዮጵያ ° " ...ድርጊቱ የደመወዝ ቅሸባ ነው ሊባል የሚችለው ፤ እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል ሰምተንም አናውቅ " - ሰራተኞች ° " ከእኛ #የሚወርደው የበጀት ሀብት እኮ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው " - የክልል ፋይናንስ ቢሮ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የመንግስት ሰራተኞች " የደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ በብርቱ ከተነሳባቸው አካባቢዎች አንዱና ዋነኛው…
#SouthEthiopia

° " የግንቦት ወር ደመወዝ እስከ ዛሬ አልወሰዱም " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር

° " ተቸግረን ያዘገየነውን የመምህራን ደመወዝ ከሰኞ ጀምረን ክፍያ እንፈጽማለን " - የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያሉ መምህራን ከደመውዝ ጋር በተያያዘ ያቀርቡ የነበሩትን ተደጋጋሚ ጥያቄ ስናቀብላችሁ እንደነበር ይታወሳል።

በተደጋጋሚ ይነሱ የነበሩ የደመውዝ ጥያቄዎች አሁን ላይ በተወሰነ መልኩ ምላሽ ቢያገኙም አሁንም ጥያቄያቸው ያለተመለሰላቸው የመንግስት ሰራተኞች በተለይ በወላይታ ዞን ያሉ መምህራን ችግር ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በተጨማሪ የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝደንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ፥ " በወላይታ ዞን ሆብቻ ወረዳ የግንቦት ወር ደመወዝ እስከ ዛሬ አልወሰዱም " ብለዋል።

ሌሎች 2 ወረዳዎች ማለትም ቦሎሶ ሶሬ እና ካዎ ኮይሻ 50% ብቻ መውሰዳቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" የመምህራን ችግር መባባሱን ተከትሎ ከዞኑ ባለስልጣናት ጋር ልንነጋገር ቀጠሮ ይዘናል " ያሉት አቶ አማኑኤል " ችግሩ በቶሎ መቀረፍ አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዜ ጎዳና ፤ ችግሩ የተፈጠረዉ ክልሉ ለማዳበሪያ ውዝፍ እዳ የሰጠዉ ትኩረት የካሽ እጥረት በመፍጠሩ መሆኑን ገልጸዉ ይህ ችግር አሁን ላይ መፈታቱን ገልጸዋል።

" የዘገየውን የመምህራን ክፍያ በጣም ባጠረ ሁኔታ ለመክፈል ገንዘብ ጠይቀን ተፈቅዶልናል " ያሉት ኃላፊው " ከተቻለ ሰኞ ጀምረን መክፈል እንጀምራለን " ብለዋል።

መምህራንም ከችግራቸዉ ይወጣሉ ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የደቡብ ክልል ፈርሶ እንደ አዲስ የተዋቀሩት #ሁሉም አዳዲስ ክልሎች በጀት የሚደለደልላቸው በነበረው የድሮ ቀመር እንደሆነ ተገልጿል። ገንዘብ ሚኒስቴር #አዲስ_ቀመር የማዘጋጀት ምንም ስልጣን እንደሌለው ይህ ስልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሆነ አመልክቷል። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የ2017 በጀት ረቂቅን ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባብራሩበት ወቅት ስለ አዳዲሶቹ ክልሎች…
የበጀት ጉዳይ !

" ' ቀመሩ እኔን ተጠቃሚ እያደረገኝ አይደለም ' የሚሉ ክልሎች እየመጡ ነው " - አቶ አገኘሁ ተሻገር

የፌዴሬሽን ም/ቤት በተለይም ከአዳዲሶቹ ክልሎች የድጎማ በጀት ቀመሩ እንዲሻሻል ጥያቄ እየቀረበለት መሆኑን የምክር ቤቱ አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናግረዋል።

አቶ አገኘሁ ፥ " ' ቀመሩ እኔን ተጠቃሚ እያደረገኝ አይደለም ' የሚሉ ክልሎች እየመጡ ነው ይሄ ቀመር እየጠቀመን ስላልሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሻሽልልን የሚል ጥያቄ እየተነሳ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በመሆኑም ም/ቤቱ ጉዳዩን በልዩ ትኩረት ተመልክቶ እምርጃ መውሰድ እንዳለበት አስገንዘበዋል።

ይህ ካልሆነ ግን ፍትሃዊ እኩል የመልማት እድል ማረጋገጥ እንደማይቻል ተናግረዋል።

ለመጨረሻ ጊዜ የክልሎች የበጀት ድጎማ ቀመር የተሻሻለው በ2010 ዓ/ም ነበር። በወቅቱ 3 ዓመት ይቆያል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ፦
- የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ
- የግብርና እና የቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ መረጃዎች አለመሟላት ቀመሩን ለማሻሻል እንቅፋት ሆኗል።

ያለፉት 30 ዓመታት የበጀት ድጎማ ቀመር ለ9 ጊዜ ተሻሽሏል። የመጨረሻው ማሻሻያ 2010 ላይ ነበር።

በቅርቡ በድጎማ በጀት ቀመር  ዙሪያ በተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ የደቡብ ክልል ፈርሶ እንደ አዲስ የተዋቀሩት ሁሉም አዳዲስ ክልሎች በጀት የሚደለደልላቸው በነበረው የድሮ ቀመር እንደሆነ ገልጸው ነበር።

ሚኒስቴሩ አዲስ ቀመር የማዘጋጀት ምንም ስልጣን እንደሌለው በመግለጽ   " ይህ ስልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው " ሲሉ ተናግረው ነበር።

በአዳዲሶቹ ክልሎች ከበጀት ጋር በተያያዘ ፤ " የበጀት እጥረት " የሚሉ ጥያቄዎች እንደሚነሱ ይታወቃል።

የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ መዘግየትና በአግባቡ አለመክፈልም በስፋትም ከአዳዲሶቹ ክልሎች የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ ከትላንትና ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ከቤትን ንብረታቸው ተፈናቅለው እስካሁን በመጠለያ የነበሩ የሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማፀብሪ ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ መጀመሩን አሳውቋል።

ከማይ ዓይኒ፣ ከማይ አንበሳ፣ ከመድኃኔዓለም እና ውሕደት ከተባሉ ቀበሌዎች የተፈናቀሉ ከአንድ ሺሕ አምስት መቶ በላይ ተፈናቃዮች ትላንት ተመልሰዋል።

ዛሬም ማይ ፀብሪን ጨምሮ የፀለምቲ ወረዳ ስድስት ቀበሌዎች ተፈናቃዮች ተመልሰዋል።

አንዳንድ ቃላቸውን ለቪኦኤ የሰጡ ተመላሾች ህዝቡ " እንኳን ደህንና መጣችሁ ! " ብሎ በመልካም ሁኔታ እንደተቀበላቸው ፤ ታጣቂዎች ግን እስካሁን እንዳልወጡ፣ ትጥቅም እንዳላወረዱ ይህ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸዋል።

ይህ አካባቢ ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ስር የጠለምት ወረዳ አስተዳደር ተብሎ ነበር።

የጠለምት አማራ ወሰንና ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ አለቃ አለነ አሰጋ ፤ " የጠለምት ወረዳ አስተዳደር የጸጥታ መዋቅር፣ ከዛሬ 3 ቀናት በፊት በግዳጅ ሥራ እንዲያቆም ተደርጓል " ብለዋል።

አለቃ አለነ ፥ በሥራ ላይ የቆየው ፖሊስ እና የጸጥታ መዋቅሩ ወደ ዓዲኣርቃይ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን ገልጸዋል።

እርሳቸው ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ግን ከአካባቢው አለመልቀቃቸውን ጠቁመዋል።

በአካባቢው የጸጥታ ስጋት መኖሩን ጠቁመው፣ መንግሥትም ይህንኑ ተገንዝቦ፣ ነዋሪው ኅብረተሰብ የራሱን የጸጥታ መዋቅር እንዲዘረጋ ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል፡፡

አለቃ አለነ የጠለምት የወሰንና የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ እንደመሆናቸው በአካባቢው ላይ ያላቸውን የወሰን እና የማንነት ጥያቄውን በቦታው ላይ እያሉ ማቅረባቸውን እንደሚቀጠሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ፌደራል መንግሥት የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው የትግራይ እና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈናቃዮች ወደቦታቸው ከተመለሱ በኃላ ከነዋሪው ህብረተሰብ ጋራ በመሆን የጋራ አስተዳደር ከአቋቋሙ በኋላ የሚነሳው ጥያቄ በሕዝበ ውሳኔ / ሪፈረንደም ምላሽ ቢያገኝ የተሻለ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ የወረቀት የነዋሪነት መታወቂያ ሙሉ በሙሉ መቆሙ ይፋ ሊደረግ ነው።

ከተማዋ በነዋሪነት ለመዘገበቻቸው ነዋሪዎች ለዘመናት በወረቀት ስትሰጥ የነበረውን የነዋሪነት መታወቂያ /City Residency ID/ ካርድ ሙሉ ለሙሉ ማቆሟን ይፋ ታደርጋለች።

አ/አ በዘመናዊ የከተማ አስተዳደር የከተማ የነዋሪነት መታወቂያን በተደራጀ መልኩ በመስጠት ከ75 ዓመት በላይ እድሜን አስቆጥራለች።

የወረቀት መታወቂያን ለመጨረሻ ግዜ ተሰናብታ ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል መሻገሯን ሰኔ 25/2016ዓ.ም ይፋ እንደምታደርግ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍጹም ሀሰተኛ / የውሸት ይዘት ነው ተጠንቀቁ " - የጠ/ሚ ጽ/ቤት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሶማሌላንድ ጋር ያደረገውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) እንደሰረዘው ተደረጎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው። የጠ/ሚ ጽ/ቤት ያወጣው መግለጫ አስመስሎ አንድ የተቀነባበረ የጠ/ሚ ጽ/ቤት አርማ ያለበት መግለጫ በስፋት እየተዘዋወረ ይገኛል። ይኸው መግለጫ ፦ - ኢትዮጵያ ከሶማሊያ…
#Ethiopia

ይህ በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስም በተለይ በ X መተግበሪያ ላይ እየተራጨ ያለው መግለጫ ሀሰተኛ እና የተቀነባበረ ነው።

የሚኒስቴሩን የቀድሞ ሎጎ በመጠቀም እየተሰራጨ ያለው ይህ መረጃ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶሌላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፦
- በUN
- በEU
- BRICS (ኢትዮጵያ እራሷ አባል የሆነችበት)
- በኢስላሚክ ሀገራት ከፍተኛ ጫና እንደሰረዘችው የሚገልጽ ነው።

ይኸው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አወጣው የተባለው መግለጫ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ፣ ቱርክ ውስጥ ለውይይት መቀመጣቸውን እና በሚቀጥሉት ቀናት የጋራ መግለጫ (ከላይ ባለው ውሳኔ) እንደሚሰጡ ያመለክታል።

ከቀናት በፊት በጠ/ሚ ጽ/ቤት ሎጎ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ሀሰተኛ መግለጫ ሲሰራጭ ነበር።

መግለጫው  በኢትዮጵያ የውጭ  ጉዳይ  ሚኒስቴር ስም በሀሰት ተዘጋጅቶ የተሰራጨ ሲሆን ያሰራጩት አካላት የመ/ቤቱን የቀድሞ ሎጎ ነው የተጠቀሙት።

ሚኒስቴሩ በመግለጫዎቹ አዲሱን ሎጎ መጠቀም ከጀመረ ወራት ተቆጥሯል።

በሌላ በኩል ደግሞ ፥ በቱርክ አግባቢነት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ቱርክ ውስጥ ለውይይት እና ንግግር እንደሚቀመጡ የሚገልጹ ሪፖርቶች ሲወጡ ነበር። ነገር ግን ምንም ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከሶማሊያ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት በይፋዊ የ X ገጹ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው በቱርክ አሸማጋይነት ከኢትዮጵያ ጋር ለሚደረግ ንግግር ወደ አንካራ ቱርክ እንዳቀኑ የሚገልጽ አንድ መረጃ ካሰራጨ በኋላ ሳይቆይ አጥፍቶታል።

ስለ ውይይቱ ሆነ እየተወራ ስላለው ጉዳይ እስካሁን ኢትዮጵያ ያለችው ነገር የለም።

#Ethiopia🇪🇹

@tikvahethiopia
2024/07/01 00:28:18
Back to Top
HTML Embed Code: