Telegram Group Search
" ካንተ ጋር ተዋህጄ ምሥጢር ከማየት የከለከለችኝ ኃጢያቴን አርቅ ዘንድ ካንተ ጋር አንድነትን ስጠኝ፤ በንጽሐ ሥጋ የሚሰጥ ልዩ ብርሃንህን በመዋሃድ ደስ ይለኝ ዘንድ፣ በንጽሐ ነፍስ በሚሰጥ ልዑል ስፉህ በሚሆን ብርሃን በንጽሐ ልቦና በሚሰጥ በረቂቅ ብርሃንህ ደስ ይለኝ ዘንድ፤ መልክህን ከማየት የሚከለክሉኝ ሰይጣናት እንዳያዩኝ፣ አቤቱ ልቦናዬ በዚህም ዓለም ግብር በማሰብ እንዳይደክም ጌትነትህን ብርሃንህን ለማየት እንድማረክ አድርገኝ፤  አቤቱ ከፍቅርህ ሊለየኝ የሚቻለው አይኑር፤  የመላእክት ክብራቸው ዕውቀታቸው ተድላ ደስታቸው፣  ሁልጊዜ ጌትነትህን የሚያመሰግኑ ሁልጊዜ በፍቅርህ የሚቃጠሉ በፍቅርህ ብርሃን ገጽ ልቡናቸው የሚያሸበርቅ፣ ከሁሉ በምትበልጥ ተዋህዶ ካንተ ጋር በመዋሃድ ፊታቸው የሚያሸበርቅ፣ እውነት ነው፤ አቤቱ ሀብታት ምሥጢራትህን  ካንተ እሻለሁ፤ አንድነትህን ሦስትነትህን የማውቅበትን ዕውቀት በልቡናዬ ትገልጽ ዘንድ እማልድሃለኁ። "

አረጋዊ መንፈሳዊ
ቅዱስ ጳውሎስን በትክክል ስለመረዳት
***
ሐዋርያው በገላትያ እና ሮሜ መልእክቶቹ ስለ 'ኦሪት ሕግ' የተናገራቸው ጉዳዮች አሉ። አነዚህን ነገሮች በትክክል ለመረዳት ሐዋርያው ከማን ጋር እየተነጋገረ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል። ጉዳዩ ከአይሁድ ዘመም ክርስቲያኖች ጋር ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ሕጉ የተሰጠበትን ዓላማ በሚገባ አና በጥልቀት ካልተረዱ ሰዎች ጋር ነው ጉዳዩ። የመጀመሪያው ያልተረዱት ጉዳይ ሕግ እስራኤልን ከሌሎች አሕዛብ ለመለየት የተሰጠው ተግባር ማብቃቱን እና አሕዛብም በአብርሃም በኩል የተገባላቸው ኪዳን መድረሱን ባለመረዳት በክርስቶስ አንድ ሆነው ሲያበቁ ከአይሁድ የመጡት ከአሕዛብ ከመጡት ለመለየት ሕጉን መጠቀም መፈለጋቸው ነው። ያ ተፈጽሞአል። ክርስቶስ እስራኤልን ከአሕዛብ የሚለየው ሕግ ፍጻሜ ነው፤ ለሁሉም መጥቶአልና። ሁለተኛው ደግሞ ሕግ ያለ ክርስቶስ ማዳን እና ጸጋ ብቻውን ሊያድን እንደማይችል በመዘንጋታቸው እና ከክርስቶስ ማዳን ጋር ማፎካከራቸው ነው። ሕግ ኃጢኣትን በመግለጥ እና መርገምን በማምጣት ለሞት አሳልፎ ይሰጣል። ይህ የሆነው ሕጉ መጥፎ ሆኖ ሳይሆን የሰው ልጅ የነበረበት የድካም ሁኔታ ያደረገው ነው። በክርስቶስ ማዳን መንፈሳዊ ጸጋ ሲሰጥ ግን ሕጉ የባርነት መሆኑ ቀርቶ 'የሕይወት እና የእምነት ሕግ' ሆነ። በቀድሞ ሁኔታው 'የሞት ሕግ' ያለውን በአዲሱ ሁኔታ 'የክርስቶስ ሕግ' እያለ መጥራት ጀመረ። በመሆኑም ሕጉ በክርስቶስ አዲስ ኃይል እና ተግባር እንዳገኘ ተናገረ። ሕጉ አሁንም እንደሚጠቅም ግን ደጋግሞ ተናግሮአል። "ኃጢኣት በሕግ ይታወቃልና" በማለት ሰዎች ኃጢኣት የሆነውን ለይተን እናውቅ ዘንድ ሕጉ የግድ እንደሚያስፈልገን ተናግሮአል። (ሮሜ. 3፥20) በመሆኑም የቅዱስ ጳውሎስ ችግር 'ቅዱስ፣ ጻድቅ እና በጎ' ብሎ ከጠራ ከሕግ ጋር ሳይሆን ሕጉን በተሳሳተ እና ግልብ በሆነ መንገድ ከተረዱ ሐሰተኛ ወንድሞች ጋር ነበር። (ሮሜ. 7፥12)
የሚያሳዘው ግን የ15ኛው መ/ክ/ዘመን የተሐድሶ አራማጆችም በዚሁ መሰናክል መውደቃቸው ነው። ቅዱስ ጳውሎስን ከትክክለኛው መልእክታቱን በጻፈበት ዘመን ከነበረው ነባራዊ ዓውድ አንጻር ሳይሆን በመካከለኛቹ ዘመናት በሮም ቤተ ክርስቲያን የነበረው ቀውስ በፈጠረው ሌላ ዓውድ ለመረዳት የመሞከር ስህተት ፈጽመዋልና።
Dn. Bereket Azmeraw

ቤተክርስቲያንን በሁለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን #በትምህርት_ዕወቃት፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን #በኑሮ_ዕወቃት። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ።

በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ። እሊህም፦ ኪዳን ማስደረስ፥ ማስቀደስና ንስሐ ገብቶ መቁረብ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው።

ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ  በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ። በሕይወትህ ሁሉ ቤተክርስቲያናዊ ሁን!

#ርዕሰ_ሊቃውንት_አባ_ገብረ_ኪዳን
እጅህ ላይ ባለው ነገር ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል።

በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቅም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል።

ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር. 12፥5

የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል።

በሕፃንነትህ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል።

በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከንዓንን ያወርስሃል።

በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል።

ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው። ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል።

አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል።በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9

(#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ)
በቤተክርስቲያን አስተምሮ በመዳን ዙሪያ ለመዳን እምነት እና ስራ አስተባብሮ መያዝ እንደሚገባን ያስተምረናል…
ማኅበረ ጽዮን
በቤተክርስቲያን አስተምሮ በመዳን ዙሪያ ለመዳን እምነት እና ስራ አስተባብሮ መያዝ እንደሚገባን ያስተምረናል ነገር ግን በእምነት ብቻ የዳኑ እንዳሉ ቅዱስ መፅሀፍ ይነግረናል። ለምሳሌ ፈያታዊ ዘይማን በተመሳሳይ 12 ዐመት ደም ሲፈሳት የነበረችውንም እምነትሽ አድኖሻል ብሏታል። ይሄንን እንዴት እንመለከተዋለን?

ለጥያቄው ምላሽ በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ


@eoteLIBRARY
ቅዱስ ጳውሎስ እና ሕግ
***
"መገረዝ ቢሆን አለመገረዝም ቢሆን ከንቱ ነው፥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጠበቅ ነው እንጂ።" (1ኛ ቆሮ. 7፥19)
ታላቁ ሐዋርያ ጳውሎስ ሆይ! መገረዝ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ስለመሆኑ ለአንተ እንዴት ይነገራል? ለአብርሃም እና ለዘሩ መገረዝን ያዘዘ ራሱ እግዚአብሔር አይደለምን? መገረዝን ከትእዛዛት ለምን አወጣኸው? ብለን እንጠይቅ። እርሱም እንዲህ ይመልሳል።
የብሉይ ሕግ ልዩ ልዩ ገጽታ አለው። አንደኛው ገጽታው እስራኤል ከአሕዛብ ርኩሰት ይጠበቁ ዘንድ ከአሕዛብ ለመለያነት የተሰጡ ሕጋት ናቸው። እነዚህም የግዝረት፣ የመባልዕት፣ የበዓላት እና የቀናት ሕጋት ናቸው። እስራኤል በሃይማኖት እስኪጎለምሱ ድረስ በመንፈስ ሕጻናት በነበሩበት ዘመን እንደ ሞግዚት ሆነው ይጠብቋቸው ዘንድ በጊዜያዊነት የተሰጡ ሕጋት ናቸው። እነዚህን ሐዋርያው በገላትያ እና በሮሜ መልእክታቱ 'የሕግ ሥራ' እያለ የሚጠራቸው ናቸው። (ገላ. 2፥16፣ 3፥2፣ 3፥5፤ ሮሜ. 3፥20፣ 3፥27 ወ.ዘ.ተ. . . ) በክርስቶስ መምጣት አሕዛብ ሁሉ የአብርሃምን ተስፋ በእምነት የሚካፈሉበት ዘመን ሲደርስ እነዚህ እስራኤልን አጥር ቅጥር ሆነው ከአሕዛብ የሚለዩ ሕጋት ተፈጽመዋል፤ ክርስቶስ የእነዚህ ሕጋት ፍጻሜ ነውና። (ሮሜ. 13፥10)
አሁን በእነዚህ የአይሁድ ሕጋት ሥር ለመሆን መፈለግ ከአዋቂነት ወደ ሕጻንነት፣ ከነጻነት ወደ ባርነት መመለስ ስለሆነ ሐዋርያው ይህን አምርሮ ይቃወማል። በዚህ መንገድ ሆነው አሕዛብ ወደ ወንጌል ለመምጣት የግድ እነዚህን የአይሁድ ሕጋት ፈጽመው 'አይሁድ' መሆን አለባቸው ብለው እዳ የሚጭኑትን አይሁድ-ዘመም መምህራን "ከክርስቶስ ተለይተው ከጸጋው የወደቁ፣ ስለክርስቶስ መስቀል እንዳይሳደዱ የሚሸሹ፣ የመስቀሉን እንቅፋት ለማስወገድ የሚሰሩ" በማለት ይወቅሳል፤ ከክርስትና ወንጌል በተቃርኖ ያቆማቸዋል። (ገላ. 5፥3፣ 11፤ 6፥12)
ሌላኛው የሕግ ገጽታ ደግሞ አይሁድን ከአሕዛብ ያለመለየት ለሁሉም የሰው ልጆች የሚሆነው እና ሕግ ያልተሰጣቸው አሕዛብ ሳይቀር በልቡናቸው የሚያውቁት፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ ከኃጢአት ተለይቶ የሚታወቅበት ነው። ቅዱስ ጳውሎስ "መገረዝም ቢሆን አለመገረዝም ቢሆን ከንቱ ነው፤" ካለ በዋላ በተጻራሪ የሚጠቅመው "የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጠበቅ ነው እንጂ፤" ብሎ የገለጸው ይህን ሰፊውን እና ጥልቁን የሕግ ገጽታ ነው።
በርግጥ ከክርስቶስ መምጣት በፊት ባሕርያችን ደክሞ ኃጢኣት ሰልጥኖ ስለነበር ሰው በሕግ ኃጢኣትን ቢያውቅም በጽድቅ መጽናት አልቻለም ነበር፤ ይልቁንም በገነት ውስጥ እንደሆነው ሕጉ ሲከለክለው እየጎመጀ ኃጢኣትን ይሠራ ነበር። የጉስቁልና ዘመን ነበርና። በዚህም የተነሣ ቅዱሱን ሕግ ራሱ ለመጥፎ መጠቀሚያ ያደርግ የነበረውን ክፉ ውድቀት ለመናገር ሐዋርያው በዚህ በሰፊ ገጽታውም ጭምር ሕጉን "የኃጢኣት ሕግ"፣ "የባርነት ሕግ"፣ "የእርግማን ሕግ"፣ "የሞት ሕግ" እያለ ጠንከር ባሉ አገላለጾች ጠርቶታል። (ሮሜ. 5፥20፣ 8፥2፣ ገላ. )
ነገር ግን ከዚህ ተነሥተው ሰዎች ወደተሳሳተ ድምዳሜ እንዳይሄዱ ደግሞ ፈጥኖ ስለ ሕጉ በጎነት እና ጽድቅ ጥብቅና ይቆማል። (ሮሜ. 7)
ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መጥቶ የሕግን እውነተኛ ገጽታ (እግዚአብሔርን እና ባልንጀራን መውደድ) በፊደሉ ሳይሆን በጥልቅ ትርጉሙ አስተምህሮ እንዲሁም በተግባር ፈጽሞ ካሳየ በኋላ፣ በሞቱ እና በትንሣኤው ባሕርያችን አድሶ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ካጠነከረን በኋላ ግን ሕጉ አዲስ ኃይል እንዳገኘ ያስረዳን ዘንድ ሐዋርያው በብዙ መልኩ ይጥራል። በአንድ ቦታ "ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና፥ እርሱም፦ ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የሚል ነው፤" በማለት ሕጉ በክርስቶስ የፍቅር ትእዛዛት እንደጸና ይናገራል። (ገላ. 5፥14) ይህንኑ ሲያመለክትም "የክርስቶስ ሕግ" እያለ ይናገራል። (ገላ. 6፥2) ቀድሞ ለኃጢኣት ኃይል መጠቀሚያ ሆኖ የነበረው በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ለጽድቅ መሆን መጀመሩን ሲናገርም "የመንፈስ ሕግ" ይለዋል። (ሮሜ. 8፥2)
***
ጠቅለል ሲደረግ የቅዱስ ጳውሎስ የሕግ አስተምህሮ ሰፊ እና መልከ ብዙ (differentiated) ነው። በአግባቡ ለመረዳት ሰፊውን ታሪካዊ እና ነገረ-ሃይማኖታዊ ዓውድ ማጤን ይገባል። ዋናው ነገር ግን ታላቁ ሐዋርያ ሕግ የሚባል ነገር አያስፈልግም፤ ተሽሮአል ብሎ አላስተማረም። የሕጉን መንፈስ እና ዓላማ እያሳየ የተፈጸመውን እና የጸናውን በየፈርጁ አስረዳ እንጂ። ሕጉን በተሳሳተ መልኩ የሚረዱትንም አወገዘ እንጂ። በተጨማሪም ሕግ ከሚፈጸምበት ጸጋ እና ሃይል ተለይቶ "ከክርስቶስ እምነት" በተጻራሪ ሊቆም እንደማይገባ በሃይለ ቃል አስተማረ እንጂ። (ገላ. 2፥16)
ቅዱስ ጳውሎስ ሕግን እንደተቃወመ አድርጎ የሚተረጎመው አካሄድ የ15ኛው መ/ክ/ዘመን የሉተር እና የሌሎች ተሐድሶዎች የተሳሳተ መረዳት (distortion) ውጤት ነው። ሉተር ጉዳዩን ይረዳው የነበረው ከቅዱስ ጳውሎስ ዓውድ አንጻር ሳይሆን ከራሱ የግል የሕይወት ቀውስ እና ከሮም ቤተ ክርስቲያን ዘመንኛ ችግር አንጻር ነበር። ይህም ትልቅ ምስቅልቅል አምጥቷል።
Bereket Azmeraw
ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶቻችን ሐዋርያትን ሰማዕትነት በተቀበሉበት ቀናት በዓላት ሰይማ ታከብራቸዋለች፡፡ እንዲሁም በስማቸው የተሰየመውን ጾም በመጾም አሠረ ፍኖታቸውን ይከተሉ ዘንድ ምእመናንን ታሳስባለች፡፡ በሐምሌ ፭ ቀን ደግሞ የደጋጎቹን ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስን በዓል ታደርጋለች፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን በዓል መደረጉ በአንድ ቀን ሰማዕትነት በመቀበላቸው ነው፡፡

ሁለቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አመራረጣቸው በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ የጥሪው መንገድ ግን ይለያይ ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት የተመረጠው ጌታችን በገሊላ ባሕር አጠገብ ሲመላለስ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ሆኖ ዓሣ ለማጥመድ መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፤ ወደ እነርሱም ቀርቦ “በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ” አላቸው፡፡ ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት፡፡ (ማቴ.፬፥፲፰‐፳)

በአንጻሩ የቅዱስ ጳውሎስ አመራረጥ ደግሞ በተአምር ነው፤ ይኸውም እንዲህ ነው፡፡ በቀደመ ስሙ ሳውል ተብሎ የሚታወቀው ይህ ሐዋርያ የቤተ ክርስቲያን አሳዳጅ ነበር፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት እስጢፋኖስ በአይሁድ እጅ ሲወገር የተስማማ የገዳዮቹንም ልብስ ጠባቂ ነበር፡፡ (የሐዋ. ፯፥፶፰-፷)

ቅዱስ መጽሐፍ “ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወህኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር፡፡ . . . ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው እየዛተ . . .” እንዲል፡፡ (የሐዋ.፰፥፫፤፱፥፩) በክርስቶስ አምነው የተጠመቁ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ከሊቁ ካህናቱ ዘንድ የፈቃድ ደብዳቤ ጠየቀ፡፡ ይህን ዓላማውን ለማስፈጸም ወደ ደማስቆ ሲጓዝ በርሱ ዙሪያ ከሰማይ መብረቅ ወረደ፤ ዐይኖቹም ታወሩ፤ ወደ ምድርም ወደቀ፡፡

በዚያም ሳለ “ሳውል ሳውል፥ ስለምን ታሳድደኛለህ” የሚለውን ድምፅ ሰማ፡፡ ያነጋገረው ሳውል የሚያሳድደው ጌታ ነበር፡፡ “አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብኻል” አለው፡፡ ከዚያም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ተነሥቶ ወደ ከተማው ገባ፡፡ ሦስት ቀንም ሳይበላ ሳይጠጣ ተቀመጠ፡፡ ሐናንያ የተባለው ከደቀ መዛሙርት ወገን የሆነ ወደ እርሱ ዘንድ ቀርቦ ጸለየለት፤ ዐይኖቹም ተፈወሱ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፡፡ (የሐዋ.፱፥፩‐፲፰)

ቅዱስ ጳውሎስ በወቅቱ ስለሆነው ነገር ለቆሮንቶስ ምእመናን ሲተረክላቸው “ ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ፡፡ እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ” እንዲል፡፡ (፩ኛቆሮ.፰፥፱)

የቤተ ሰብ ሕይወታቸው
ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ቤተ ሰቦቹ ደግሞ በቅፍርናሆም ይኖሩ ነበር፡፡ የኦሪት መጻሕፍትን ያልተማረ ከዝቅተኛው የማኅበረሰብ ክፍል የተገኘ ሰው ነበር፡፡ (የሐዋ. ፬፥፲፫) ጳውሎስ ደግሞ በኪልቅያ በምትገኘው በጠርሴስ ተወለደ፡፡ ከአይሁድ ወገን ከብንያም ወገን ነበር፡፡ (ፊል.፫፥፭) በጠርሴስም ሳለ በገማልያል እግር ሥር የኦሪት ትምህርቱን ተማረ፤ በትምህርቱም የተመሰከረለት ነበር፤ (የሐዋ.፳፪፥፫፤፳፮፥፳፬) ይህ የሚያሳየው የእግዚአብሔር መንግሥት ለተማሩትም ላልተማሩትም፣ ለባለጸጎችም ለድሆችም የተዘጋጀ መሆኑን ነው፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስ ባለ ትዳር ነበር፡፡ አማቱም ታማ በነበር ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤቷ ገብቶ እንደፈወሳት በወንጌል ተጽፏል፡፡ (ማቴ.፰፥፲፬‐፲፭) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ድንግል ነበር፡፡ “ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁና ነገር ግን፥ እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ፡፡ ላላገቡና ለመበለቶች ግን እላለሁ፡- እንደ እኔ ቢኖሩ ለእነርሱ መልካም ነው፤ ነገር ግን፥ በምኞት ከመቃጠል መጋባት ይሻላልና፥ ራሳቸውን መግዛት ባይችሉ ያግቡ” በማለት ለቆሮንቶስ ምእመናን ጽፏል፡፡ (፩ኛቆሮ. ፯፥፯‐፱) ቤተ ክርስቲያን እንደ ጴጥሮስ ያገቡ እንደ ጳውሎስ ያሉ ደናግላንን ይዛ የምትገኘው ጌታችን ሁሉንም ወደ እርሱ ስለጠራ ነው፡፡

የስማቸው መለወጥ
ቅዱስ ጴጥሮስ የዮና ልጅ ስምዖን ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ (ዮሐ.፳፩፥፲፭) ነገር ግን ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን “እናንተስ ማን ትሉታላችሁ” ብሎ ሲጠይቃቸው ሐዋርያው ተነሣና፡- “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብሎ መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም ጌታችን “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፡፡ እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም አለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም” በማለት ጴጥሮስ ብሎ ሰየመው፡፡ (ማቴ.፲፮፥፲፯—፲፰)

ጳውሎስን ደግሞ ጌታችን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲጠራው በመጀመሪያ ስሙ ሳውል ብሎ ጠራው፤ በምስክርነቱ ጊዜ ደግሞ “ጳውሎስ ሆይ፥ በኢየሩሳሌም ስለ እኔ እንደ መሰከርህ እንዲሁ በሮሜም ትመሰክርልኝ ዘንድ ይገባሃልና፥ አይዞህ አለው፡፡” (የሐዋ.፳፫፥፲፩)

አገልግሎታቸው
የቅዱስ ጴጥሮስ አገልግሎቱ በአብዛኛው ሕግ ለተጻፈላቸው፣ ነቢያት ለተላኩላቸው፣ መሥዋዕት ለሚያቀርቡ፣ ግርዛት ለተሰጣቸው ለአይሁድ ነበር፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የቅዱስ ጳውሎስ አገልግሎት የነበረው በአሕዛብ መካከል ነበር፡፡ ይህንንም ሲመሰክር “ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን ሠርቷልና፡፡” ብሏል፡፡ (ገላ.፪፥፯‐፰) እንዲያውም በአንድ ወቅት ጳውሎስና በርናባስን አይሁድ ትምህርታቸውን በተቃወሟቸው ጊዜ “እነሆ ወደ አሕዛብ ዘወር እንላለን እንዲሁ ጌታ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ አዞናልና” ብለው ነበር፡፡ (የሐዋ. ፲፫፥፵፮—፵፯)

በበዓለ ኀምሳ ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበሉ በኋላ ጴጥሮስና ዮሐንስ በትምህርታቸው በኢየሩሳሌም ለነበሩ ነፍሳት ደረሱ፡፡ በአንድ ቀን ብቻ ሦስት ሺህ ነፍሳት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተጨመሩ፡፡ (የሐዋ.፪) ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ “ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ” በማለት ስለተሰጠው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ መስክሯል፡፡ (፩ኛቆሮ. ፲፬፥፲፰) ሁለቱም ሐዋርያት በምእመናን ላይ እጃቸውን በመጫን ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ያሳድሩ ነበር፡፡ (የሐዋ.፰፥፲፬፤፲፱፥፭‐፮)

በአገልግሎታቸው ድንቅ ተአምራትን ፈጽመዋል፡፡ ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡፡ “እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥ ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር፡፡” (የሐዋ.፲፱፥፲፩—፲፪) በኢዮጴም ጣቢታ የምትባል አገልጋይን ከሞተች፤ አጥበውም በሰገነት ከአኖሯት በኋላ ቅዱስ ጴጥሮስ ካለበት ተጠርቶ ከጸለየ በኋላ ጣቢታ ሆይ ተነሽ ሲላት ዐይኖቿን እንደከፈተች ተጽፏል፡፡ (የሐዋ.፱፥፴፮—፵፪) በተመሳሳይ ቅዱስ ጳውሎስ አውጤኪስ የሚባል ከሦስተኛ ደርብ ወደ ታች ወድቆ የሞተን ጎልማሳ እንዲነሣ አድርጓል፡፡ (የሐዋ.፳፥፯—፲፪)
መልእክታት
ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት መልእክታትን ለምእመናን ጽፏል፤ ቅዱስ ጳውሎስ በአካል ተገኝቶ ለሰበካቸውና ላጠመቃቸው የሮሜ፣ የቆሮንቶስ፣ የገላትያ፣ የኤፌሶን፣ የፊልጵስዩስ እና የቆላስይስ፣ የተሰሎንቈ፣ ለዕብራውያን ምእመናን መልእክታትን የጻፈ ሲሆን ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቹ ለጢሞቴዎስ፣ ለቲቶ እና ለፊልሞና መልእክታትን ሰዶላቸዋል፤ በአጠቃላይ ዐሥራ አራት መልእክታትን ጽፏል፡፡

ሰማዕትነታቸው
ሁለቱም ቅዱሳን ሐዋርያት በሮማው ቄሳር ኔሮን ዘመን ፷፯ ዓ.ም. ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነት የተቀበለ ሲሆን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ አንገቱን ተቀልቶ ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡
በረከታቸው ይደርብን፤ አሜን!

Mahebere kidusan
እያንዳንዱ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 10/

እንኳን ለበዓለ ጴጥሮስ ወጳውሎስ አደረሰን አደረሳችሁ።

በቅዳሴያችን ወቅት ገባሬ ሠናይ ዲያቆኑ ከጳውሎስ መልእክት ካነበበ በኋላ በዜማ የምንለው መርግፍ እንዲህ ይላል። “ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ ሠናየ መልእክት ፈዋሴ ዱያን ዘነሣእከ አክሊለ ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ ያድኅን ነፍሳተነ በብዝኀ ሣህሉ ወምሕረቱ በእንተ ስሙ ቅዱስ” – ‘አክሊልን የተቀዳጀህ፣ ድውያንን የምትፈውስ፣ መልእክትህ ያማረ፣ ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ ሆይ በይቅርታውና በቸርነቱ ብዛት ስለ ቅዱስ ስሙም ብሎ ነፍሳችንን ያድን ዘንድ [ወደ ጌታ] ስለእኛ ለምንልን፣ ጸልይልንም’ ማለት ነው።

በዚህች አጭር ጸሎት እንዲያደርግልን በምታሳስብ አጭር ልመና ውስጥ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት በአጭሩ የሚገልጹ ሦስት ነገሮች ተቀምጠዋል። ድዋያንን የሚፈውስ፣ መልዕክቱ ያማረ መሆኑና በዚህም አክሊል የተቀዳጀ መሆኑን የሚያሳዩ ወሳኝ መግለጫዎች ናቸው።

ቅዱስ ጳውሎስ በሁለንተናው ፈዋሴ ዱያን ነውና ዛሬም ቤተ ክህነታችን ከተያዘበት፣ የዘረኝነት፣ የጠባብነት፣ የሌብነት፣ የአላዋቂነት፣የፖለቲከኝነት እና ለሹመት የማበድ በሽታ ይፈውስልን።

መልእክቱም በእውነት በእጅጉ ያማረ ነው። በቆሮንቶስ መልእክቱ ላይ “የእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ፥ ሌላውም በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ። ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፥ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤ በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፥ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል። ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤ የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 10 -15/ ሲል የገለጸውን እና እኛ ካለንበት ሁኔታ አንጻር ላለው የሚጠቅም የሚመስለኝን እንኳ ብናየው መልእክቱ ምንኛ ያማረ ነው። 

ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ሐዋርያት የሠሩት የቤተ ክርስቲያን መሠረት የማይለወጥ ማንም ፈላስፋም ሆነ ፖለቲከኛ፣ ጎልበተኛም ሆነ ሴረኛ ሊለውጠው የማይችል ንጹሕ ሐዋርያዊ መሠረት ነው ያለን። ከእነርሱ በኋላ የመጡት ግን ሐዋርያው እንዳለ በወርቅ በብር እና በከበረ ድንጋይ ያነጹ ቢኖሩም አንዳንዶቹ ደግሞ በገለባ፣ አንዳንዶቹም በሣር ሌሎቹም ደግሞ በእንጨት በጭራሮ የሚያንጹ ነበሩ። እኛ ሀገር በዚህ ወቅት የምናየው የዘር ቤተ ክህነት እና የጎሳ ጵጵስና ጉዳይ በሣር እና በአገዳ ያንጻሉ ያላቸውን የሚያስታውስ ነው። እንዲህ በእንጨት፣ በሣር፣ በአገዳ የሚያንጹት ቢኖሩም ቤተ ክርስቲያን ግን ጸንታ ትኖራለች ። በእግዚአብሔር የፍርድ እሳት ሲመረመር የእነርሱ ይቃጠላል፣ የባለ ብሮቹ እና የባለወርቆቹ የተባለው የንጹሐኑ ሥራ እና ተጋድሎ እና የመሳሰሉት ግን የበለጠ ይጠራል፣ ያበራል፣ ይከብራል። 

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በየዘመኑ ስለሚኖር እና አሁንም ስላለነው ሲናገርም “በትልቅም ቤት የእንጨትና የሸክላ ዕቃ ደግሞ አለ እንጂ የወርቅና የብር ዕቃ ብቻ አይደለም፥ እኵሌቶቹም ለክብር፥ እኵሌቶቹም ለውርደት ይሆናሉ” /2ኛ ጢሞ 2 ፡ 20/ ሲል የገለጸውም ምንኛ ያምራል። እውነት ለመናገር በትልቋ ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የክብር ዕቃ ዓይነት የከበሩ ሰዎች ቢኖሩም ግን ደግሞ መናኛ እና የውርደት ዕቃዎች በተባሉት የምንመሰል ሥራችን ሁሉ ተዋርዶ ማዋረድ የሆንንም እንኖራለን። ዘንድሮ እያየን ያለውም ይህን ይመስለኛል። ተዋርደው የሚያዋርዱ መንደርተኛ ሿሚዎች እና ተሿሚዎች፣ ደጋፊ አሽቃባጭ የጥፋት ቲፎዞዎች እና አጨብጫቢዎች ። ቅዱስ ጳውሎስ የሚለን በተልቅ ቤት ውስጥ ይህ ሁሉ ሊኖር የግድ ነው ነው የሚለን። ይህ ነገር ሁልጊዜም የነበረ እና ያለ ቢሆንም ዘንድሮ የምናየው ግን በትልቁ ቤት በእግዚአብሔር ቤት በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ዕቃው ሁሉ እጅ ሲነካው ቅድድ የሚል፣ ትንሽ ሙቀት የሚያቀልጠው የያዘውን ነገር እንኳ በወጉ የማያደርስ፣ የሽክል ዕቃ ያህል እንኳ ስባሪው የማይገኝ የእኛኑ ዘመን ስስ ፌስታል የሆንን ይመስለኛል። እውነቱን ለመናገር በየቤታችን ያለውን የኬንያን የፕላሲክ ዕቃ ያህል እንኳ ወግ መዓርግ ማጣታችን በእጅጉ ያሳዝናል። እንኳን የወርቅ እና የብር ዕቃ መሆን የሸክላ ዕቃ መሆንን እንዳቃተን ሳስብ እንኳ እገረማለሁ። ነገር ግን መልእክቱ ያማረው ያ ምርጥ ሐዋርያ እንዳለው በትልቁ ቤት በእግዚአብሔር ቤት ግን ይህ ሁሉ ይኖራል ተብሏልና ቢያንስ መደነቅ የለብንም።

ቅዱሱ ሐዋርያ ባዛሬው ዕለት ለእውነት ፣ እውነት ለተባለው ለክርስቶስ ተሰውቶ አክሊል ተቀዳጅቷል። አሁን የእርሱን ሥልጣን የሚፈልጉት ደግሞ የየጎሣ ዘውድ ለመቀዳጀት ይጣደፋሉ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጥሶ ለመሾም ይሯሯጣሉ፣ ይፎክራሉ፣ ይሸልላሉ። ከሁሉ የሚገርመኝ ደግሞ ይህን በማድረጋቸው ያሸንፉ፣ ያጎዱን፣ በንዴት ያቃጠሉን መስሏቸው ሲደስቱ እና ሲደልቁ ስመለከት  እውነተኛው ዕብደት ምን እንደሚያደርግ እየገባኝ እገረማለሁ። በርግጥ በእብደት ውስጥ ያለ እብደቱ ገብቶት አያውቅም። እንኳን ያበደ፣ ለጊዜው እእምሮውን የሳተም ምን እንደሆነ የሚጠይቀው ከተሻለው በኋላ ነው። እውነቱን ለመናገር አሁን በትግራይ የሚታሰብውን ሳስብ ደም ያሰክራል የሚለው ነው ወደ አእምሮየ የሚመጣው። በተለይ አንዳንዶች ይልቁንም የዚሀ ጉዳይ አቀንቃኞች በርግጥም ተጎድተዋል፣ ደም አስክሯቸዋል። ፈዋሴ ዱያን የተባለው ቅዱስ ጳውሎስ ይፈውሳችሁ ከማለት በቀር ሌላ ምን ይባላል። ሰው ከእግዚአብሔር ቃል እና ሕግ ይልቅ እንዴት ለፖለቲከኞች ጭልጥ ብሎ ያታዘዛል? የእነርሱን ለብቻው የምጽፍበት ስለሚሆን አሁን አልነካካም። ለሁሉም ግን አእምሮው ጨርሶ ያልጠፋበት ካለ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ማንም ቢሆን እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ።
Dn. Birhanu Admas
Audio
ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት
        
Size:-35.6MB
Length:-1:42:08

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
በዓለ ቅድስት ሥላሴ

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ!

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን! የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! የሐምሌ ሰባት በዓለ ቅድስት ሥላሴን በተመለከተ አጭር ጽሑፍ አቅርበንላችኋል፤ ተከታተሉን!

በዚህችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት ቅድስት ሥላሴ በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ። የይስሐቅንም ልደት አበሠሩት ባረኩት፤ አከበሩትም። (መጽሐፈ ስንክሳር ዘሐምሌ ሰባት)

አብርሃም አባታችን በተመሳቀለ ጎዳና አራት በር ያላት ግንብ ሠርቶ ያለፈውን ያገደመውን የወጣውን የወረደውን ሲቀበል ይኖር ነበር:: ሰይጣን በዚህ ቀንቶበት ግንባሩን ገምሶ፣ ልብሱን፣ ገፎ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ልብሱን በደም ለውሶ ሄዶ፡፡ ወደ አብርሃም ቤት መሄጃ መንገድ ላይ ተቀምጦ ወደ አብርሃም ቤት እንግዳ ሲመጣ “ወዳጄ ወዴት ትሄዳለህ?” ይለዋል፤ “ወደ አብርሃም ቤት” ይለዋል:: “አይ አብርሃም የቀድሞው አብርሃም መሰለህ? እኔ ያጎርሰኛል፤ ያለብሰኛል ብዬ ብሄድ ይኼው እንደምታየኝ ግንባሬን ገምሶ፣ ደሜን አፍሶ ሰደደኝ፤ እኔን ያገኘ መከራ እንዳያገኝህ ይቅርብህ፤ ባትሄድ ይሻልሃል” እያለ እንግዳ መለሰበት::

ከዚህ በኋላ አብርሃም “ማዕደ እግዚአብሔር ያለ ምስክር እንዴት ይቀርባል?” ብሎ ሦስት ቀን ጾሙን አደረ። ቅድስት ሥላሴ ርኅሩኃን ናቸውና በእንግዳ ልማድ ሄደው ከደጁ ከመምሬ ዛፍ ተቀምጠው አያቸው፤ እርሱም ሊቀበላቸውም እየሮጠ ወጣ፤ በቀረበም ጊዜ ወደ ምድር ሰገደ፤ “አቤቱ በፊትህ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባርያህን አትለፈኝ ብዬ በእውነት እለምንሃለሁ፤ ከቤቴ ገብታችሁ ዕረፉ” አላቸው:: “በፊትህ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባርያህን አትለፈኝ” ብሎ መናገሩ አንድነቱን፣ ጥቂት ውኃ ይምጣላቸሁ እግራችሁን ታጠቡ ብሎ መናገሩ ሦስትነታቸውን ለመግለጽ ነው:: ይህ ምሳሌ ነው፤ ዛፏ የእመቤታችን ምሳሌ ናት፤ ሥላሴ በዛፏ ሥር ተቀምጠው እንደ ታዩ አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ ለተዋሕዶ በእመቤታችን የማደራቸው ምሳሌ ነው:: ይህቺ ዛፍ በአብርሃም ደጃፍ ተተክላ፣ ቅርንጫፎቿን አንሰራፍታ ቅድስት ሥላሴን ለመቀበል እንደበቃች፣ እመቤታችንም ከአብርሃም ዘር ተወልዳ፣ ጸጋዋ ተንሰራፍቶ፣ ክብሯ፣ ልዕልናዋ ሰፍቶ የሥላሴ ማደሪያ ለመሆን በቅታለችና፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “አንቲ ውእቱ ዕፀ ድርስ ዘለአብርሃም በርስአኒሁ ዘብኪ አጽለለ እግዚአብሔር በሥላሴሁ፤ለአብርሃም በእርጅናው ወቅት እግዚአብሔርን በሦስትነት ያስጠለለብሽ የወይራ ዛፍ አንቺ ነሽ” በማለት ገልጾታል:: (እንዚራ ስብሐት)

ቅድስት ሥላሴም “አዝለህ አግባን” አሉት ጽንዐ ፍቅሩን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም አንዱን አዝሎ ሲገባ ሁለቱን ገብተው አግኝቷቸዋል! አብርሃም ሣራን “ሦስት መስፈሪያ ዱቄት አምጥተሸ በአንድ አድርገሽ ጋግሪ” አላት፤ እርሷም እንዳዘዛት አደረገች፤ “ወአቅረበ ሎሙ መዓረ ወዕቋነ ወእጓለ ላህም ስቡሓ፤ ድፎ ዳቦ አቅርቦላቸዋል፤ ላህም ሠውቶላቸዋል” ባርከው አስነሥተውለታል! ሕያዋን እንደሆኑ ለማጠየቅ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ልጅ እንደሚወልድ ነግረውት ሲሄዱ ከሦስቱ አንዱ “የዛሬ ዓመት በእውነት ወደ አንተ እመጣለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅ ትወልዳለች” ብሎ ተስፋውን ነግሮት ሄደዋል:: (ዘፍ.፲፰፥፲)

ቅድስት ሥላሴ በእንግዳ አምሳል የገቡት በቤተ አብርሃም መስተናገዳቸውን ቅዱስ ያሬድ ሲናገር “አብርሃም ርእየ ሠለስተ እደወ በዛቲ ዕለት ምሥጢረ ሥላሴ ዜነወ እትነሣእ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ውእቱ ኀይልየ አምላኪየ ረዳእየ ወመድኀንየ፤ አብርሃም ሦስት አረጋውያንን ተመለከተ፤ በዚያች ዕለት የሥላሴን ምሥጢር ተናገረ፤ አብና ወልድ መንፈስ ቅዱስ ኀይሌ፣ አምላኬና መድኀኒቴ ነው ብዬ እነሣለሁ” በማለት የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ተገልጦለት እንደተናገረ ሊቁ በዜማው መስክሯል:: (ድጓ ዘሥላሴ ኆኅተ ሰብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ገጽ ፭፻፰፯)

ይስሐቅን ሳይወልድ አብራም ይባል ነበር፣ አበ ውሁዳን ማለት ነው፡፡ ይስሐቅን ከወለደ በኋላ ግን አብርሃም ተብሏል አበ ብዙኃን ማለት ነው፡፡ (ዘፍ.፲፯፥፮ አንድምታ ትርጓሜ)

አባታችን አብርሃም ይስሐቅን ሳይወልድ “አብራም” ይባል ነበር፤ “አበ ውሁዳን” ማለት ነው፡፡ ይስሐቅን ከወለደ በኋላ ግን “አብርሃም” ተብሏል፤ “አበ ብዙኃን” ማለት ነው፡፡ ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እግዚአብሔር ለአብርሃም ምሥጢር እንደገለጠለት ሲናገር “አብርሃምን መረጠው ወዳጄም አለው፤ የተሰወሩ ምሥጢራትን ሁሉ ገለጠለት፤ አብርሃም እንደ ፀሐይና እንደ ንጋት ኮከብ ብሩህ እንደሆነ በመንፈስ ቅዱስ ሁሉንም ነገር ነገረው” ሲል ዘምሯል፡፡ (ድጓ ዘሥላሴ፣ ኆኅተ ሰብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቀጽ ፪ ገጽ ፭፻፰፯)

ስለዚህ በአብርሃም በኩል ምሥጢሩን ለገለጡለት ለቅድስት ሥላሴ ምስጋና እንደሚገባ ሲናገር “ንግሩ ምሕረቶ ለሥላሴ ወዜንዉ ሠናይቶ ለሥላሴ መሃይምናን ንግሩ ምሕረቶ ለሥላሴ፤ የሥላሴን ምሕረቱን ንገሩ፤ የሥላሴ በጎነቱን መስክሩ! እናንተ ምእመናን የሥላሴ ምሕረቱን ተናገሩ” በማለት ያሳስባል።

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው። በዚህ ጊዜ ተገኙ፤ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም፤ መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸው። እንግዲህ ሥላሴ ስንል፦

*ሥላሴ ዋሕድ* በአንድ እግዚአብሔር ከሚገኝ ከሦስቱ አካላት ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ በቀር፥ ቅድመ ዓለም ቢሆን ፣ ድኅረ ዓለማት ቢሆን ፈጽሞ ሌላ መንቲያ ወይም ተመሳሳይ የሌለውና ብቻውን የሚኖር ልዩ ሦስት "ሦስትነት" መሆኑን የሚያረጋግጥ አብነት ነው።

ሃሌ ሉያ ለአብ ፥ሃሌ ሉያ ለወልድ፥ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋሕድ።

*ሥላሴ ዘለዓለም (ዘለዓለም ሥላሴ)* ይህ ሲባል የሥላሴ መጠሪያ ስም ከጊዜ በኋላ የተገኘ ሳይሆን ከዘለዓለም በሥላሴነቱ የነበረ ያለ የሚኖር መሆኑን የሚታወቅበት ገለጻ ነው። እምቅድመ ዓለም ወእስከ ለዓለም ሀሎ እግዚአብሔር በትሥልስቱ፤ እግዚአብሔር ከዓለም በፊት እስከዘለዓምም ድረስ እግዚአብሔር በሦስትነቱ አለ፡፡ (ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ)

*ሥሉስ ቅዱስና ልዩ ሦስትነት* ይህ ሦስትነት አንድነት ያለው በመሆኑ ሥሉስ ቅዱስ ይሰኛል ማለት ሦስት አካላትን የያዘ ቅዱስ የተለየ ባሕርይ ያለው እግዚአብሔር ወይም መለኮት ማለት ነው።

*ልዩ ሦስትነት* የእግዚአብሔር ልዩ ሦስት ሲባል በሦስትነት በአንድነት የሚገኙ ልዩ ምሳሌዎች አሉና ከዚያ ለይቶ ለማስገንዘብ ነው። ከእነዚህም አንዱ የአካል ሦስትነት ቢኖራቸውም የባሕርይና የህልውና አንድነት የላቸውም። ለምሳሌ “አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ” ብለን የምንጠራቸው ሦስት ስሞች ናቸው።

እንደዚሁም ደግሞ በአንድ የአካል ስም ሲጠሩ በኩነታት ሦስትነት ያላቸው አሉ። እነርሱም ፀሐይ፣ እሳት፣ ቀላይ፣ ባሕር፣ ተክልና ንፋስ ናቸው። የሰው ነፍስ ብትሆንም እንኳን የኩነት፣ የግብር ሦስትነት አላት እንጂ የአካል ሦስትነት የህልውና አንድነት የላትም።
ሥላሴ ግን የአካል፣ የግብር፣ የኩነት ሦስትነት፥የመለኮት የባሕርይ የህልውና አንድነት አላቸው። ልዩ ሦስት "ቅድስት ሥላሴ" ይባላሉ።

ዳግመኛም ሥላሴ፡-
ወላድያነ ዓለም “ቅዱስ” ሥላሴ ማለት ትተን “ቅድስት” ሥላሴ ብለን በሴት አንቀጽ እንጠራቸዋለን፤ የምንጠራበት ምክንያት ምንድን ነው? ስንል ስለ ብዙ ምሥጢር ነው፤ እንደ ሊቃውንቱ ትንታኔ ሴት ርኀርኅተ ልብ ናት፤ ሥላሴም ለፍጥረታቸው ርኅሩኃን ናቸውና፡፡ አንድም ሴት ከባሕርይዋ ልጅ ትወልዳለች! ሥላሴም ወላድያነ ዓለም ናቸው፤ ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር ካለመታየት ወደ መታየት አምጥተው የፈጠሩ ፈጥረውም የሚያስተዳድሩ ቅድስት ሥላሴ ናቸውና:: አንድም ጽኑዕ፤ ንጹሕ፣ ክቡር፣ ልዩ ሲል ነው፡፡ ሰውን ጽኑዕ ቢሉት እስከ ጊዜው ነው፤ እንጂ ኋላ በሕማም በሞት ይለወጣል:: ቅድስት ሥላሴ ግን መቼም መች ሕልፈት ውላጤ ድካም ሕማም የለባቸውም፡፡

አምልኮት መሠረት

ቅድስት ሥላሴ የአምልኮታችን መሠረት ነው፤ ይህ ማለት ምስጋናም ሆነ አምልኮት የሚጀመረው በቅድስት ሥላሴ ነው፤ የማንኛውም አገልግሎት መክፈቻም ሆነ መዝጊያ የቅድስት የሥላሴ ስም ነው! ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎቷን “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ” ብላ ጀምራ “ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ” ብላ ትዘጋለች::

ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲናገር “ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ አአትብ ወእትነሣእ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሠለስተ አስማተ ነሚእየ እትመረጐዝ እመኒ ወደቁ እትነሣእ ወእመኒ ሖርኩ ውስተ ጽልመት እግዚአብሔር ያበርህ ሊተ በእግዚአብሔር ተወከልኩ፤ ቅድመ ዓለም የነበረ ዛሬም ያለ ወደ ፊትም ዓለም አሳልፎ የሚኖር በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተነሥቼ አማትባለሁ፤ እነዚህን ሦስት ስሞች ይዤ እመረኮዛለሁ፤ ብወድቅ እነሣለሁ፤ ወደ ጨለማ ብሔድ እግዚአብሔር ያበራልኛል፤ በእግዚአብሔር ታመንኩ” ሲል የሃይማኖታችን መነሻና መድረሻ ቅድስት ሥላሴ መሆኑን መስክሯል:: (ድጓ ዘሥላሴ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ገጽ ፭፻፹፰)

ዳግመኛም ቅድስት ሥላሴ የአምልኮታችን መሠረት የእምነታችን ምንጭ እንድሆነ ሊቁ ግልጥ አድርጎ ሲነግረን “ነአምን ወናመልክ በአሐዱ እግዚአብሔር ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ ወነአምን በካልዑ እግዚአብሔር ዘበምልክናሁ ለአብ ይመስሎ ወነአምን በሣልሱ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዘይመልዕ፤ ቅድመ ዓለም በነበረ በአንዱ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን እናመልካለን፤ አብን በጌትነት በሚመስለው በሚተካከለው በእግዚአብሔር ወልድ እናምናለን እናመልካለን፣ በዓለም ምሉዕ በሆነው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን እናመልካለን” ሲል ቅድስት ሥላሴ የአምልኮታችን ማዕከል መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ (ድጓ ዘሥላሴ)
የሚሠዋው መሥዋዕት፤ የሚጸለየው ጸሎት፣ የሚታጠነው ዕጣን የሚቀርበው ቁርባን ሁሉ የሚያርገው ወደ ቅድስት ሥላሴ ነው:: ሊቁ እንዲህ እንዳለ “አንትሙሰ ከመ ዕብነ ሕይወት ተሐነጹ ቤቶ ለመንፈስ ቅዱስ ወለክህነቱ ቅዱስ ከመ ታዕርጉ መሥዋዕተ ወትንግሩ ሠናይቶ፤ ለቅዱስ አገልግሎት ሕያው መሥዋዕትን ታሣርጉ ዘንድ በጎነቱን ትነግሩ ዘንድ፣ እናንተ እንደ ሕይወት ድንጋይ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ሆናችሁ ታነጹ” በማለት ዘምሯል፡፡ (ድጓ ዘሥላሴ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ገጽ ፭፻፹፰)

ሙሴ የያዛቸው ሦስት ስሞች

ሊቀ ነቢያት ሙሴ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ወደ ከነአን ሲጓዝ ለጉዞው መሳካት የእግዚአብሔርን ረድኤት የሚጠይቅበትና ሕዝቡ ሲበድሉ የእግዚአብሔርን ምሕረት የሚማፀንበት ሦስት ስሞች ነበሩ፡፡ እነዚህን የያዛቸው ሦስት ስሞች ደጋግሞ መጥራት የፈጣሪውን ምሕረትና ረድኤት አግኝቷል፤ እነዚሀ ሙሴ የያዛቸው ስሞች ምንድን ናቸው? ሙሴ በአብርሃም፣ በይስሐቅ፣ በያዕቆብ ስም ፈጣሪውን ይማጸን እንደነበር ተናግሯል፡፡ እነዚህ ሦስት ስሞች የሥላሴ ምሳሌ ናቸው፤ እነዚህ ስሞች የቃል ኪዳን ማስታወሻ ናቸው፤ እግዚአብሔር ለጊዜው ምድራዊቷ ርስት ከነአንን እንደሚያወርስ፣ ለፍጻሜው ደግሞ ሰማያዊቷን ርስት ወደ መንግሥተ ሰማያትን እንደሚያወርስ ከሕዝቡ በረድኤት እንደማይለይ ቃል ኪዳን ይገባ የነበረው በእነዚህ ስሞች ነበር፤ ሕዝቡም ለአብርሃም ለይስሐቅ ለያዕቆብ የገባውን ቃል ኪዳን አስቦ የእግዚአብሔር ልብ እንዲራራላቸው ያደርጉ ነበር።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ይገልጠዋል “መፍቀሬ ሰብእ ክርስቶስ ፈኑ ሣህለከ ወምሕረተከ ዘአንተ ታርኁ ክረምተ በጸጋከ ወትሴሲ እመዝገብከ ስብሐት ለከ ወዐቢይ ኀይልከ ዘሠራዕከ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ ዘሠርዐ ለአብርሃም ወመሐለ ለይስሐቅ ወዐቀመ ስምዐ ለያዕቆብ ንስእለከ ወናስተበቊዐከ እስመ ኵሉ ዘሥጋ ያንቃዓዱ ኀቤከ፤ ሰው ወዳጅ ክርስቶስ ሆይ ይቅርታህንና ምሕረትህን ላክ፤ አንተ ክረምትን የምትከፍት፣ ከመዝገብህ በጸጋህ ትመግባለህ፤ ምስጋና ለአንተ ይገባል፤ ኀይልህ ታላቅ ነውና፤ ለዕረፍት ሰንበትን የሠራህ፤ ለአብርሃም ለይስሐቅ የማልክ፤ ለያዕቆብ ምስክርነትን ያቆምክ” ሲል ዘምሯል፡፡ እነዚህ ሦስት ስሞች (አብርሃም ይስሐቅና ያዕቆብ) የእግዚአብሐር ሕዝብ የመሆን ምልክት ነበሩ፤ ሥላሴም የሃይማኖት ምልክት ናቸውና፡፡ (ድጓ ዘሥላሴ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ገጽ ፭፻፹፱)

ቅዱስ ያሬድ ሲናገር “ነሡእየ ማዕተበ ዘወልደ እግዚአብሔር አአትብ በሥላሴ እመኒ ወደቁ አቲብየ እትነሣእ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኀይለ መስቀሉ እትመረጐዝ፤ የወልደ እግዚአብሔርን የኢየሱስ ክርስቶስ ምልክት የኾነውን ቅዱስ መስቀል ይዤ በሥላሴ ስም አማትባለሁ፤ ብወድቅ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አማትቤ እነሣለሁ፤ በመስቀሉም እመረኮዛለሁ” ሲል ዘምሯል:: (ድጓ ዘሥላሴ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ገጽ ፭፻፹፱ )

በአጠቃላይ ምሥጢረ ሥላሴን በሚገባ መርምሮ መረዳት ለማንም ቢሆን አይቻለውም። እርሱ ባወቀ ግን በብዙ አይነት በብሉይ ኪዳንም ይልቁንም በሐዲስ ኪዳን ምሥጢረ ሥላሴን እራሱ ባለቤቱ በጥምቁቱ ገልጦልናል፡፡ ይህንንም በዓል ሰናከብር እግዚአብሔር (ሥላሴ) በአብርሃም ቤት ተገኝተው፣ የአብርሃምን ቤት በርከው ሊመጣ ያለውን የሐዲስ ኪዳን ነገረ ድኅነት በግልጥ ነገሮናል። እኛም በዓሉን ሰናከብር እምነታችን በቅድስት ሥላሴ ላይ በማድረግ በቀናች ሃይማኖት ልንጸና ይገባናል!

እንደ አብርሃም ንጹሕ ልብ ይዘን፣ ከኀጢአት ርቀን እንግዶችን እንድንቀበል አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን፤ አሜን!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ በሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ
አምስቱ አዕማደ ምሥጢር በምኑን በኀበ ሰብእ
ሃይማኖተ አበው ተስፋ ገብረ ሥላሴ
ምሥጢረ ምሥጢራት በገብረ መድኅን እንየው እና መዝገበ ቃል ገ/ሕይወት

Mahebere kidusan
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እግዚአብሔርን የኢትዮጵያ ብቻ አምላክ ማድረግ አደገኛ ነው

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ነገረ ሃይማኖት 101
***
በአመክንዮአዊነት የታጠረ፣ በተወሰኑ ፎርሙላዎች ላይ የቆመ፣ ወጥ በሆነ መንገድ በቀላሉ ማብራራት የሚቻል (coherently explainable) ነገረ-ሃይማኖታዊ ሐተታ ስታይ የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ ተረዳ። የክርስትና ነገረ-ሃይማኖት ከአመክንዮ ጋር የሚቃረን ባይሆንም ከሰው መረዳት የሚያልፍ እና በጥቂት አመክንዮአዊ ሐተታዎችና ፎርሙላዎች የማይጠቃለል ምሥጢር አለው። መለኮታዊ ስለሆነ!
በመሆኑም ሰዎች በአመክንዮአቸው ልክ ቀንሰው የሰፉት (reductionist) ትምህርት የሚቀረው ብዙ ነገር አለ፤ ስህተትን ያስከትላል።
የምዕራቡ ዓለም ክርስትና በመካከለኛው ዘመን ክርስትናን በአርስቶትላዊ አመክንዮ ውስጥ ለመቀመር ሞክሮ ብዙ ተጎድቷል። የእኛም ሊቃውንት በዚህ አልተፈተኑም ማለት ይከብዳል። በተለይ በአንዳንድ 'ሊቃውንት' ነገረ-ክርስቶስ የሚብራራበት የመገናዘብ ሐተታ (communication of idioms) የተለጠጠ እና አመክንዮአዊ ትምክህት የሚታይበት ነው። ይህ ወደ ችግር እንጂ ድኅነት የሚወስድ አይደለም። ነገረ-ክርስቶስ የመዳን ምሥጢር ነው። ክብር ይገባዋል።

Bereket Azmeraw
የመዳን_ትምህርት_በዘመናት_ሂደት_ውስጥ_አጭር_ዳሰሳ_በዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ.pdf
204.5 KB
የመዳን ትምህርት በዘመናት ሂደት ውስጥ - አጭር ዳሰሳ

* የነገረ ድኅነት ትምህርት በምዕራቡ አለም
* ስኮላስቲሲዝም (scholasticism)
* የትሬንት ጉባኤ
* የፕሮቴስታንቶች አጸፌታ
* ኦርቶዶክሳዊ የመዳን ትምህርት

++++++++ ~ +++++++

መዳን ከኃጢአት ይቅርታ ባሻገር ብዙ ነገሮችን የያዘ ሰፊና ጥልቅ ነገር ነው፡፡ ስለዚህም አንደኛውንና የመጀመሪያውን ሥጦታ (የኃጢአትን ይቅርታ ማግኘትን) ብቻ ሌላውን እስከሚያስረሳ ድረስ ማጉላትና ከዚያ ያለፈ ነገር የሌለ ማስመሰል እግዚአብሔር የሰጠውን ጸጋ ማሳነስና የተጠራንበትን ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን ጥሪ ማስረሳት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱሳዊውና በአበው ቀደምት አስተምህሮ መሠረት መዳን ስንል ሥርየተ ኃጢአት ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ማወቅን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ማግኘትን፣ ብርሃናዊነትን ገንዘብ ማድረግን፣ ከባርነት ነጻ መውጣትን፣ አዲስ ተፈጥሮንና የጸጋ አምላክነትን ገንዘብ ማድረግን ሁሉ የሚጨምር ሰፊና ጥልቅ ነው::

++++++++ ~ ++++++++

ኦርቶዶክሳውያን አባቶቻችን የጸጋው ሥጦታ ነጻ (እንዲሁ) የሚሰጥ መሆኑን በአንድ በኩል፣ የሰውን ነጻ ፈቃድ (ነጻነት) ደግሞ በሌላ በኩል አስተባብረው በመያዝ ለሰው መዳን የሁለቱ መስተጋብር (በግሪኩ Synergy) አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ያስተምራሉ፡፡ ይህም በቅዱስ ጳውሎስ “ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና” ተብሎ የተገለጸው ነው፡፡ 1 ቆሮ. 3:9


#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
2024/07/20 20:44:15
Back to Top
HTML Embed Code: