Telegram Group Search
❤️ነፍሴ ስትመክረኝ …

የውስጥ ሰላም ከብር ፣ ከወርቅ ፣ ከአልማዝም ሆነ እንቁ ይልቃል ፤ ስኬታማነት ከውስጥ ሰላም ፣ ደስታና ፍቅር በጥብቅ የተቆራኘ ካልሆነ ትርጉሙ ጎዶሎ ነው። ወደ ሀቅ የምትጠራህ ነፍስህን በድለህ ሺህ ግዜ የምድር ሃብት ብትሰበስብ ሀብትም ሆነ ሌላ ነገርህ የውስጥ ሰላም እስካላስገኘልህ ድረስ ተሳካልህ ተብሎ አይታመንም ፤  በዚህ መልኩ የምታገኘው ነገር " ይዘህ ተገኘህ " እንጂ ተሳካልህ አያሰኝም።.

📍ሰላም የሚያሳጡ ፍጡራኖችን ያየህ እንደሆነ በሌሎች ሰዎች ዋጋና መስዋትነት ማትረፍ የለመዱ ፤ ከራሳቸው ጋር ሰላም መፍጠር ያልቻሉ ስግብግቦች እንደሆኑ  ለሰከንድ አትጠራጠር። ከእንደዚህ ዓይነት ስግብግብነት ተጠቆጠብ የሰላም እሴትህን ጠብቅ ፣ ይዘው የተገኙት እየቀደሙህ እየመሰለህ የመልካምነት ጉዞህ መሐል ላይ አትወዛገብ ከመልካምነት እና ከሀቅ በላይ አድካሚና አሸልቺ ግን ደግሞ ፍሬው ጣፋጭ የሆነ እፁብ ድንቅ መታደልና መባረክ የለም።

💡አንዳንድ ጊዜ በራስህ ዓለም ዉስጥ ብቻ ለመኖር ሞክር፡፡፡ ወደ ምድር የመጣኸው ትርጉም ላለው ዓላማ ነውና ሁሉም ቦታ ላይ ጥቀም፡፡ በደረስክበት ቦታ ሀሉ መልካም ዝራ፡፡

📍እቅድህን በመኖር ሂደት በሚገጥሙህ ፈተናዎች አታማር ከአሁን ቀደም የሆኑ ፣ እየሆኑ ያሉ ፣ ከአሁን በሁዋላ በፈለግከውም ሆነ ባልፈለግከው መንገድ የሚሆኑ ነገሮች ሁሉ በምክንያት ያጋጠሙህ እንደሆኑ እመን። የፈተና መብዛቱ ለበጎ ነው፡፡ አካሄድህን እንድታስተካክል ይረዳሃል፡፡ በችግሮች ዙሪያ ተጠበብ እንጂ አትጨነቅ ፤ ለመልካምነትና ከሀቅ ጋር ለመታረቅ የረፈደ የሚባል ግዜ የለም ፤ የቻልከዉን ያህል ስራና እረፍ ፤ ቀሪውን ለፈጠረህ ጌታ ተወው።

ሀቀኝነትን ድፈር ፤ ሀሜተኝነትንና ዋሾነትን ፍራ

💡ደፋር ይሰማል ፣ ያደምጣል ፣ ይናገራል ፣ ይመረምራል ፣ ይፅፋል ፣ ይወስናል ፤ የሰማውን ሁሉ እንደ ሰነፎችና ፈሪዎች እውነት ብሎ አያምንምም አይፈርጅምም ፤ የሰማኸውን ሁሉ እንደ እውነት አምነህ ደግመህ ደጋግመህ ሳታረጋግጥ አታውራ ፤ ማጣራትን አስቀድም ፤ ሳትጠይቅ እና ሳታመዛዝን አትፍረድ።

ስምህን ከምታውቀው በላይ እርግጠኛ ሁን

💡እንዲህ ስታደርግ ሁሉም የሚታየው ጭለማ ፣ የሚያወራው ስለጭለማ ቢሆን ላንተ የሚታይህ ብርሃን እንጂ ሌላ አይሆንም። አትጠራጠር ንስር አሞራ ፈተናዎቿን ከደመናው በላይ ከፍ በማለት እንደምትሻገረው አንተም ፈተናዎችን ከችግሮች በላይ ከፍ ብለህ በማለፍ የውስጥ ሰላምህን ቀጣይነት እያረጋገጥክ ማሳካት ወደ ምትፈልገው ግብ የማትደርስበት ቅንጣት ታክል ምክንያት አይኖርም።

📍እናም እየነዳን ወዳጆቼ

ሁሉንም ነገር በንቃት እየታዘብን እስከነዳን ድረስ  ፤ በችግር ውስጥ ሆኖ በመሳቅ ፣ በደስታ እና በውስጥ ሰላማችን እስካልተደራደርን ድረስ የማንሻገረው ፈተናና የማናሳካው  ግብ አይኖርም።

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

💫እንኳን ለ 1445ኛው የዒድ አል ፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
                
❤️በመላው አለም የምትኖሩ የእስልምና እምነት ተከታይ ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛው የዒድ  በአል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን።

የዒድ በአል የእዝነት ÷ የመተሳሰብ ÷ አብሮ የመብላትና የመፈቃቀር በአል በመሆኑ በየ አካባቢያችን በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን እያሰብን እንዋል።

          ዒድ ሙባረክ !!!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
💎አንተ ከነሱ የተለየህ በመሆንህ ሲስቁብህ አንተ ደግሞ አንዳይነት በመሆናቸው ሳቅባቸው!

ንስር የጨለመውን ወጀብ ሰንጥቆ ያልፋል እንጅ ጨለማው እስኪያልፍ አይጠብቅምና ጀግናም ጥዋት በወጣበት ስታይል አይመለስም ለማለት ነው ። 😉

አለም ለደፋሮች ታደላለች። ወደ ከፍ ያለ ማንነት ጉዞ ስትጀምር የነፍስክ ጥንካሬ ተአምራዊ ወደ ሆነ ቦታ ያደርሥሀል።

ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ ትሁንልን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
🌗በአንድ ወቅት ጫካ ውስጥ መውለጃዋ የቀረበ አንዲት ሚዳቆ የመውለጃ ሰዐቷ ደርሶ ትግል ላይ ሳለች ድንገት አከባቢዋን ስትቃኝ ከፊት ለፊቷ ወንዝ ፣ ከኋላዋ ቀስት ያነጣጠረባትን አዳኝ፣ ወደ ጎን ስትዞር የተራበ አንበሳ አሰፍስፎባት ትመለከታለች።

ይህም ሳይበቃት ጭማሪ ከፍተኛ ነጎድጓድና መብረቅ ያጀበው ደመና መጥቶ ሰማዩን ያጨልመዋል። መብረቁም ሀይለኛ ስለነበር ደኑን ይመታውና ከፍተኛ ቃጠሎን ያስነሳባታል። ምን ታድርግ?

ወደ ፊት ሮጣ እንዳታመልጥ ጥልቅ ወንዝ ተደቀነባት፤ከኋላዋ አዳኙ፤ከጎኗ ደግሞ አንበሳው፤ወደ ጫካ ገብታ እንኳ እንዳትደበቅ ደኑ ከፍተኛ ቃጠሎ ላይ ነው...
በዚያ ላይ የውልደት ህመም ነፍስ ውጪ ግቢ እያስባላት ነው ...

💡ሚዳቆዋ በዚህ ውጥረት ውስጥ ሆና ትኩረቷን መፈፀም ወደ ምትችለው ነገር ላይ ብቻ በማድረግ ቀሪውን ለፈጣሪ በመተው በመወለድ ላይ ስላለው ልጇ ብቻ ማሰብ ጀመረች.....

አዳኙ ቀስቱን አነጣጥሮ ሊለቅ ባለበት ቅፅበት ድንገት የመብረቁ ብልጭታ አይኑ ላይ ብዥታ ፈጠረበትና ቀስቱ ተስፈንጥሮ ወደ ተራበው አንበሳ ይሄድና አንበሳውን ይገለዋል።

አጉበድብዶ የነበረው ደመናውም መዝነብ ይጀምርና የደኑን ቃጠሎ በቅፅበት አጠፋው። በጭንቅ ታጅባ የነበረችው ሚዳቆም በሰላም ተገላገለችና ወደ ቀደመው ህይወቷ ተመለሰች።

🔑አንዳንዴ በህይወትህ ውስጥ በብዙ ፈተናዎችና ጭንቀቶች ልትከበብ ትችላለህ፣ ያኔ አንተ ልትፈታው በምትችለው ነገር ላይ ብቻ አትኩርና ቀሪውን ለመፍትሄዎች ሁሉ ባለቤት ለሆነው ለፈጣሪህ ተወው።

መውጫ መፍትሄ አንተጋ እንጂ ፈጣሪህ ዘንድ አይጠፋም። አስታውስ ሁሌም ትላልቅ ወይም ከባባድ ፈተናዎች አሉብኝ ብለህ ለፈተናዎች እውቅና ከመስጠትህ ይልቅ የከባባድ ፈተናዎች አለቃ የሆነው ፈጣሪ አለኝ እያልክ ጭንቀቶችህን አቅልላቸው፣ሁሌም በፈጣሪህ ፈፅሞ ተስፋ አትቁረጥ!!!

📍ገጣሚ በረከት በላይነህ ''ሳይፀልዩ ማደር'' በምትለው ውብ ግጥሙ እንለያይ፣

''ሳይፀልዩ ማደር''

የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋ ፀለየች....
"አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
...
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
ሚዳቆዋን አይቶ - አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው - አምላኩን ጠየቀ
...
የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ ከበረታው ጠላት"
...
ነብሩንም አለው - "እሩጥ ተከተላት ምግብ አድርገህ ብላት"
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
.
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛው ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
...
አውጣኝ ያለው ወቶ አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ

           ውብ አሁን ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
💡ቀላል የህይወት መንገድ  ምርጫህ ሆኖ ጠንካራ፣ ስኬታማና ምርጥ ህይወት የሚኖር ሰው አትጠብቅ።

💡በመከራዎቹ ሁሉ ተፈትኖ እንደወርቅ ቀልጦ የምርጥ ማንነት ባለቤት የሚሆነውን ፣ ጠንካራውን፣ አይበገሬውንና የህይወት መንገድ ነፃነቱን በስኬቱ የሚጎናፀፈውን አንተን ለመተዋወቅ ሁሌም ረጅሙና ፈታኙ መንገድ ምርጫህ ይሁን።

   በረጅም ድካም የማይገኝ ነገር የለምና

          ውብ የስኬት ጊዜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
🔴ብርጭቆህን ባዶ አድርግ!!

ቻይና ውስጥ አንድ በጣም ጠቢብ የዜን ፍልስፍና (Zen Philosophy) መምህር ነበር።  ሰዎች የእርሱን እርዳታ ለማግኘት እና ጥበብ ለመቅሰም  ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ይጓዙ ነበር።  

አንድ ቀን አንድ የተማረ (ምሁር) ምክር ለማግኘት መምህሩን ይጎበኛል።   ምሁሩም ስለ ዜን የህይወት ፍልስፍና ለመማር እንደመጣ ይናገራል።

🔹ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ውይይቱ ተጀመረ። ምሁሩ አእምሮው ‘በሁሉን አውቃለሁ ባይነት’ የተሞላ እና በእራሱ አመለካከት፣ አስተሳሰብ  እና እውቀት ፍፁምነት  ያምን ነበርና በንግግራቸው ወቅት መምህሩ የሚናገረውን እና የሚያስተምረውን ከመስማት እና ትኩረት ከመስጠት ይልቅ የራሱን ታሪክ እና ስለ ምሁርነቱ በማውራት መምህሩን የመናገር እድል ይነሳዋል። 

🔹መምህሩም በእርጋታ አንድ ላይ ሻይ እንዲጠጡ ሐሳብ ያቀርባል። ለእንግዳው (ምሁሩ) ባቀረበው ብርጭቆም ሻይ ይቀዳለታል።  ብርጭቆው ሞላ። 

🔹ነገር ግን መምህሩ እየፈሰሰም ቢሆን ሻይውን መቅዳቱን አላቆመም። ጠረጴዛው ላይ እስኪፈስ ድረስ ሻይ እየቀዳለት ነበር።  ሻይው ወለሉ ላይ ብሎም በምሁሩ ጃኬት ላይም ይፈስ ነበር።   ምሁሩም በመገረም እየተመለከተው ‘’“ተው እንጅ!  ብርጭቆው እኮ ሞልቷል።  ማየት አትችልም እንዴ ” ይላል።

🔸መምህሩ በፈገግታ “ብርጭቆህን ባዶ አድርግ! አንተም  ልክ እንደዚህ ብርጭቆ ሁሉ አእምሮህ ባረጁ ሃሳቦች እና እምነቶች የተሞላ ስለሆነ ከዚህ በላይ ምንም አዲስ እውቀትና ሃሳብ መቀበል አቁመሃል። ‘’ በማለት ተናግሮ ብርጭቆውን ባዶ አድርጎ እንዲመለስ መከረው።  .

እኛም በህይወታችን ውስጥ በየቀኑ ተመሳሳይ ታሪክ ይከሰታል። ሁሉንም የምናውቅ ይመስለናል እናም ‘በትህትና ማዳመጥ እንዲሁም ከሌሎች መማር አያስፈልገንም!’ ብለን አእምሮአችንን ሞልተን ባዶ ማድረግ አቅቶናል!!!

🟢In Zen we don't Find the Answer , We loose the question" የምትል ግሩም አባባል አላቸው። ራስህን ባዶ አርገህ መማር ከፈለክ ዙሪያህ ሁሉ አስተማሪ ነው!  ሩቅ ሳትሄድ ከጎንህ ላለው ሰው ልብህን ክፈት፣ በመጠየቅ በመመለስ ሳይሆን በመረዳት እና በማስተዋል ነው አብርሆት የሚፈጠረው።

🟡የሰው ልጅ የነብሱን መንፈሳዊ ጎዳና ትክክለኝነት ማወቅ የሚችለው መንገደኛው ራሱ ነው..ስለ ሕይወትህ ችግር ከገጠመህ ወይም ጥያቄ ከተፈጠረብህ ዙርያህን አጥና... ያለህበት ሁኔታ ከሕይወትህ ጋር ያለውን አንድምታ መርምር በተለይ ትንሽ ትልቅ ሳትል በአቅራብያህ ያሉ ሰዎችን ህይወት በመመልከት ላንተ ምን መልእክት እንዳለው በትጋት ተከታተል ምክንያቱም የተፈጥሮ መንፈሳዊ አንደበት ናቸውና..."

🔴የተፈጥሮን መንፈሳዊ ቋንቋ ተማር ስትወድቅ ሆነ ስትነሳ ፍቺው ምን እንደሆነ ውስጥህን ጠይቅ  እውቀትን ሩቅ ፍልስፍና ወይም አንቃቂ ዲስኩሮች ውስጥ አትፈልግ፣ ከራስህ ጀምር ምክንያቱም የኩራዝ ብርሃንን ብታይ በደንብ የሚያበራው አቅራብያው ላለው ነው። አንተም ለራስህ ብርሀን ሁን መማር አታቁም፣ እድገትህን አትግታ፣ እራስህን አሻሽል፤  በአዳዲስ እውቀቶች እራስህን አንፅ!

ሁሌም ብርጭቆህን ባዶ አድርገህ ተነስ!

        ውብ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
❤️ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ:-

እንኳን ለጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!

በዓሉ፦ የሰላም ፣ የፍቅር፣ የደስታ ፣ የመተሳሰብ ፣ የአብሮነት እና የአንድነት በዓል እንዲሆን እንመኛለን።

  (መልካም ትንሳኤ ፤ መልካም በዓል!)❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
📍‹‹በቂ›› ስንት ነው? (How much is enough!

🔷ጊዜ በቂ አይደለም፡፡ ሕይወት በቂ አይደለም፡፡ ዕውቀት በቂ አይደለም፡፡ ገንዘብ በቂ አይደለም፡፡ ደስታችንም በቂ የሚባል ደረጃ ላይ አልደረሰም፡፡  ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በቂ ነው አይባልም፡፡ የዚህ ዓለም ፍቅርም በቂ አይደለም፡፡ አብዛኛው የዘንድሮ ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በወረት ያጠረ እንጂ ዘላቂ አይደለም፡፡

🔶‹‹በቂ›› የሚለውን ቃል በሁለት ፊደል ብቻ መወከል ፍትሐዊ አይደለም፡፡ በቂ እንደየሰዉ መስፈሪያ ከፍም ዝቅም ይላል እንጂ እቅጩን ሆኖ አያውቅም፡፡ የምንም ነገርን መስፈሪያ በግምትና በስምምነት ወይም ከዚህ እስከዚህ የምንለው እንጂ በራሱ በቂ የሆነ አይደለም፡፡ በቂ የመጠን ጉዳይ ነው፡፡ መጠንን መመጠን ደግሞ የመጣኙ ፋንታ ነው፡፡ አንዱ ከመጠኑ አስበልጦ አሙልቶ ሲያፈሰው ሌላው ደግሞ ከመጠኑ በታች አድርጎ ያጎድለዋል፡፡ በቂን የሚያበቃው በአዕምሮ የበቃው ብቻ ነው፡፡

♦️ኑሮ ያልበቃን፣ ገንዘብ ያልበቃን፣ ዕውቀት ያልበቃን፣ ደግነት ያልበቃን፣ ፍቅር ያልበቃን የምንፈልገውን የእውነት ስለፈለግነው ሳይሆን ሌሎች ስለፈለጉት ብቻ እኛም ሰለፈለግነው ነው፡፡ አዎ ብዙዎቻችን የምንፈልገውን የማናውቀው ፍላጎታችን የተመሰረተው በሌሎች ፍላጎት ላይ በመሆኑ ነው፡፡

🔹በእርግጥ መሠረታዊው የሰው ልጅ ፍላጎት ተመሳሳይ ቢሆንም አፈላለጋችንና ፈልገን የምናመጣበት መንገድ የተለያየ ነው፡፡ የሆድ ጉዳያችን፣ ርሃባችን፣ ጥማችን ስሜቱ የጋራ ቢሆንም መንፈሳዊ ረሃባችንና ጥማታችን፣ እንዲሁም አስተሳሰባችንና ግባችን የተለያየ ነው፡፡ የብቃት መለኪያችንም የሚለየው ‹‹በቂ›› የሚለው መስፈሪያ እንደየአስተሳሰባችን አንድ ወጥ ባለመሆኑ ነው፡፡

ሮበርት ስኪደልስኪ የተባለ ፀሐፊ እንዲህ ይላል፡-
‹‹የምንፈልገው ከመጠን በላይ ስለሆነ አይደለም፡፡ ነገር ግን እኛ የምንፈልገው ሌሎች ከሚፈልጉት የበለጠ እንዲሆን ስለምንሻ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ሌሎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የሚፈልጉት እኛ ከምንፈልገው በላይ እንዲሆን ነው፡፡ ይሄም መጨረሻ ወደሌለውና አሸናፊው ወደማይለየው ፉክክር ውስጥ ከትቶናል፡

🔶በመጠን ኑሩ!! ከዕውቀት ሁሉ ዕውቀት ፦ መጠንን ማወቅና ‹‹በቂ››ን መገንዘብ ዋነኛ የህይወት ጉዳይ  ነው፡፡ ከመጠን ያነሰም ሆነ የበዛ ጣጣ አለው፡፡ ከበቂ በላይም ሆነ ከበቂ በታች ሁሉቱም አይጠቅሙም፡፡ በቂ መካከለኛው ነጥብ ነው፡፡ በቂ መጠን ነው፤ መጠን ደግሞ ማስተዋል ነው፡፡

🔷ወዳጄ ሆይ የብልፅግና ዋነኛ ግብ መሆን ያለበት እንደገብጋቦች ማከማቸት ሳይሆን ሕይወትን በምድር ላይ በደስታ ማኖር ነው ። አንድ ሰው ሀብታም ነው ሚባለው ደሞ ባለው ነገር ሲረካና በቃኝ ሲያውቅ ብቻ ነው። አንተም መጠንህን እወቅና ብቃትህን ተጎናፀፍ፡፡ የምትፈልገውን ሁሉ ለማሟላት ስትል ዕድሜህን አትጨርስ፡፡ ከምትፈልገው ይልቅ የሚያስፈልግህን ምረጥ፡፡ ማግበስበስን ሳይሆን መመጠንን ልመድ፡፡ የ‹‹በቂ›› መስፈሪያህን በቅተህ አግኘው፡፡

        በቂ ሕይወትን ተመኘን!
           ውብ ቅዳሜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
🔴 ስኬት የደስታ ቁልፍ አይደለም ይልቁንስ የስኬት ቁልፍ ደስታ ነው ! ምክንያቱም የምንሰራው ስራ ከወደድንው ስኬታማ ና ውጤታማ የማንሆንበት ምንም አይነት ምክንያት አይኖርም ፣ ደስታችን ከስኬታችን ያደርሰናል !

🔶በሞያህ ደስተኛ ከሆንክ የምታስበው
ስኬት ወደ አንተ ይመጣል፣ በምትሰራው ነገር ደስተኛ ከሆንክ ከጥሩ ነገር ትሰራለህ ከጥሩ ቦታ ትደርሳለህ ውጤትን ታገኛለህ፣ ስኬት ማለት ያለህበት ቦታ ሳይሆን የምታስበው የምታስበው ነገር ነው ፣ ስዎች ራሳቸው የወሰኑትን አለያም ያሰብትን ያክል ደስተኞች ናቸው !
እያንዳንዱ ሰው የሚደሰተው በዘጋጅው የደስታ መጠን ያክል ነው ።

🔷ደስተኛ የሚያደርግህ ያለህ ነገር ማንነትህ ያለህበት ቦታ አለያም የምትሰራው ስራ ሳይሆን የምታስበው ነገር አስተሳሰብህ ነው ! ምክንያቱም ደረጃህን የሚወስነው አቋምህ ሳይሆን አስተሳሰብህ ስለሆነ !ማንነታችንን ተቀብለን ከራሳችን ጋር ሰላም እስካልፈጠርን ድርስ ባለን ነገር ደስተኞች አንሆንም !

🔶ፈጣሪህን ታመን። ልብ በል ፤ ቤትህን በፍጥነት ሠርተህ መጨረስህ ሳይሆን ንፋስና ጎርፍን መቋቋም የሚችል ጠንካራ አድርገህ መሥራትህ ነው ቁምነገሩ። በሰዎች ደስታ ደስ ይበልህ። የእውቀት ሰውና ጠንካራ ሠራተኛም ሁን! በዕውነት ፣ በሃቅና በራስ አገዝ አዋጭ መንገድ ከተራማድክ እመነኝ በያንዳንዱ እርምጃህ ስኬትህን እየገነባህ ነው።

🔷 ስኬት በቅንነት እንጅ በብልጠት አይደለም ! ሊሆንም አይችልም። አጭበርብሮ ስኬት ከመቆናጠጥ በክብር መውደቅ ይሻላል፣ የምትሔድበት የስኬት መንገድ ሺህ ጊዜ ይርዘም እንጂ ቶሎ ለመድረስ ብለህ አቋራጭ መንገድ አትጠቀም። ልብህ በእውነት ላይ ተረማምደው በሰዎች ትከሻ ላይ ተንጠልጥለው ፣ በአቋራጭ ባደጉ ሰዎች እንዳይቀና! የግፍንም እንጀራ እንዳትበላ ተጠንቀቅ ፣ትግስትን ገንዘብህ አድርጋት አምላክ ለአንተ ያዘጋጀዉ ነገር አለውና።

እናም ወዳጄ

የስኬት መጨረሻ የውድቀት መጀመሪያ እንደሌለ እወቅ ፣ ስኬት በተገኘ ነገር ላይ በመርካት እንደሚለካ አስብ። ስኬትን ከአእምሮ እርካታ ጋር እንጂ ከቁስ ጋጋታ ጋር አታዛመድ፣ የሰው ልጅ እራሱን ሊያስደስት የሚችለው በመልካም ባህሪውና በሚሰራው ጥሩ ሥራ እንጂ የሚያምር መልክና አቋም ወይንም በርካታ ሀብት ስላለው አይደለም ... የሚያምር አቋምህና ሀብትህ ምድር ላይ ቀሪ ናቸው ..መልካም ስራህ ግን ለነገ ስንቅ ይሆንሐል ! ባለህበት  የህይወት ደረጃ መርካት ከቻልክ በራሱ ስኬት እንደሆነ እወቅ።

                ውብ አሁን ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@Ethiohumanitybot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📍አንዳንዴ ምን ሆነሀል ስትባል የማትመልሰው ብዙ መሆን አለ። ለመናገር የማይመች ለመተው የማይቀል ብዙ ስሜት አለ ..ለአንተ የከበደ ለሌላው የቀለለ ነገር አለ ።

💡እንዴ ይሄ እኮ ቀላል ነው ይሄ እኮ አያስጨንቅም በሚባል ቃል የሚሸነፍ ለአንተ/አንቺ ግን የከበደ ስሜት አለ ።
ምን ሆነሀል ስትባል ምንም ብለክ የምታልፈው ውስጥህ ብቻ የምታንሸራሽረው እያዳመጥክ የምትታመምበት ። ከባድ ስሜት አለ ከባድ.......

❤️ምናልባት የምትፈልገው ስፍራ ላይ አልተቀመጥክ ወይንም የምትመኘውን ነገር አላገኘህ ይሆናል፣ ቢሆንም ተስፋ አትቁረጥ ፣ ተስፋ የመኖር ምክንያት ነውና፣

እየኖርን ነው አይደል? በሰው ሳይሆን በፈጣሪ!!
ትላንት የኖርነው ህይወት በነበር ይተካል፣
ሰዎችም ኖረው ነበሩ ይባላሉ፣
ፈጣሪን ግን ነበር ብለን አናወራውም ፤ ያለና የሚኖር ፣ በዛሬያችን ,በነጋችን አልፎም በዘላለም ውስጥ ኗሪ ነው ።
" የትላንት ነበሮቻችን በእሱ መኖር ተረስተዋል"

እናም ወዳጄ

አትድከም ፣ አትዘን ። ማንያውቃል ሸክምህ ህመምህ ሁሉ ተራግፎ ሌላ ሰው ሆነህ ትነሳ ይሆናል። ያለን ፈጣሪ እንኳን በአንድ ሙሉ ቀንና ሌሊት፣ በቅጽበት ጊዜ ዉስጥም ብዙ ተዓምር ይሠራል።

💡ንፋስ የማይወዘዉዘው ዛፍ የለም። ችግር ፣ ፈተና ፣ ሀሳብ ወስዶ የማይመልሰው ሰዉም የለም። እንዲህም ሆኖ የማይወድቅ ዛፍ አለ። በፈተና የሚፀና የሚበረታ ሰዉም አለ። ዐሳብህ ጉልበትህ ሥሮችህ ታክቶዋቸው በደከሙ ጊዜ ልብህ ብቻ ፈጣሪን ይዞ ይበርታ።

          ውብ ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
💎የመሰብሰብ ጉጉትህ ላይ እስካልሰለጠንክ ድረስ የሚበቃ ነገር የለም፤ ጊዜ በጨመረ - ቀን በተቆጠረ ልክ የፍላጎት አድማስ እየሰፋ፣ የመጨመር ሃሳብ እየተንሰራፋ ይቀጥላል...

💡የመጨመር ጉጉት ጉድለት ላይ ብቻ ከመቆዘም የሚፈጠር ህመም ነው፤ በቃኝ አለማወቅ ልክን የመሳት አባዜ ነው... ምን 'ሀብታም' ብትሆን በፍላጎትህ ላይ ገዢ እስካልሆንክ ድረስ የደስታን ደጅ አትረግጥም...

📍በሕይወት ውስጥ በቃኝ የማለትን ያህል ምልዓት የለም!! ብዙ ሰው "ያለኝ ይበቃኛል" እያለ ያጣቅሳል - እንደ ጥቅሱ ግን አይኖርም፤ ጥያቄው ታዲያ 'ያለው ስንት ሲሆን ነው የሚበቃው?' የሚለው ነው፤

የኑሮ ቅንጦት የበዛበትም፣ መኖር ቅንጦት የሆነበትም እኩል 'ያለኝ ይበቃኛል' ካለ ልክ አይሆንም... ስሜትም አይሰጥም።

📍ቁምነገሩ 'ያለህ መብቃቱ' ሳይሆን ባለህ መብቃቃቱ ነው... ሁሉም ሰው 'ያለኝ ይበቃኛል' ሲል 'የሚገባውን' ብቻ ይዞ ላይሆን ይችላል... የተትረፈረፈለትም - ትራፊ ያጠጠበትም አንድ ሊሆን አይችልም... ግና የሚብቃቃ ሰው በውስንነት ውስጥ ሆኖም ጉድለት አይሰማውም...

💎ስትብቃቃ ያለህ ምንም ያህል ይሁን ደስታ ሳይርቅህ ትኖራለህ፤ ስታግበሰብስ ግን ምድሪቱ ሙሉ ስጦታ ሆና ብትቀርብልህ እንኳ በቃኝ አያውቅህም...አንተ ዘንድ የበዛው ከሌላው ጎድሎ ነው፤ በማትፈልገው ጊዜ በስብሶ ሳትጥለው በሚፈልገው ጊዜ ለሚጠቀመው ስጠው!!

ደምስ ሰይፉ
@BridgeThoughts
[የግል ቻናሉ ነው ተቀላቀሉት ]

ውብ አዳር ❤️

@Ethiohumanity
@EthioHumanity

@EthiohumanityBot
🛑 ኢኮኖሚክስ ላይ 'Water & Diamond paradox' የሚባል እሳቤ አለ... ለኑረት ወሳኙ ነገር ውሃ ነው ፣ ግን 'እርካሽ' ነው። አልማዝ ለህላዌ የሚያበረክተው ድንቡሎ የለም  ግን ውድ ነው። ለዚህም ይመስላል አንስታይን "The important things are always simple" ማለቱ...

ዘግይቶም ቢሆን የሚገባህ እውነት ነገሮችን በውድና ርካሽ የሚፈርጀው አስተሳሰብ እንጂ የነገሩ ወሳኝነት አለመሆኑ ነው። እርግጥ ማሕበረሰባዊ ስምምነቶች ለተፈጥሮ ህግ ከመገዛት ይልቅ መንጋነትን ያበረታሉ።

ለምሳሌ፦
፨ ዋናው ቁምነገር አብሮነትና ፍቅሩ ቢሆንም ውዱ ግን ሰርጋችን ነው...
፨ ትልቁ እውቀት ራስን ማወቅ ቢሆንም ውዱ ግን ከአስኳላ የምንገዛው ነው።
፨ ጠቃሚው ውበት ጸጥታ ቢሆንም የምንከፍለው ግን ለሚበጠብጠን ጩኸት ነው።
፨ ጤናችን ያለው ንጹህ ውሃ ውስጥ ቢሆንም ብዙ የምንከፍለው ግን ለመታመሚያችን አልኮል ነው... ወዘተ

እልፍ ርቀት ሮጠህ ስታበቃ ቆም ብለህ 'ለዚህ ጉዳይ ይህን ያህል ዋጋ መክፈል ነበረብኝን?' ብለህ ብትጠይቅም መሮጥህን ግን አታቆምም።

በዙሪያህ ያሉ ነገሮች ጡዘትህን እንጂ ቆምታህን አያበረቱም ፣ ይልቁን በውድድር ውስጥ እንድትቆይ ይገፉሃል ከጓደኛህ ትወዳደራለህ ፣ ከጎረቤትህ ትወዳደራለህ፣ከባልደረባህ ትወዳደራለህ ፣ ከንግድ አቻዎችህ ትወዳደራለህ... እናም በምስሉ ላይ እንደምታየው ማቆሚያ በሌለው ዙረት [Vicious circle] ውስጥ ትቧችራለህ።

📍ዛሬ የሆነ ነገር ለማግኘት ትሮጣለህ... ደርሰህ ስትይዘው ይቀልብሃል፣ነገ ሌላ ለመጨበጥ ትዘረጋለህ፣ ደርሰህ ስታየው 'ለዚህ ነው በሬዬን ያረድኩት?' ያስብልሃል... እንደገና ሌላ ሩጫ. እንደገና ሌላ ፍለጋ... እንደገና ሌላ መባከን...

እጅህ ላይ ያለው ካላስደሰተህ እርግጠኛ ሁን ሊመጣ ያለውም አያረካህም። በበርህ አበባ ሳትፈነድቅ በገነት ውበት አትመሰጥም። ደስታን ከውጭ ከመፈለግ በላይ ጉድለት የሚመስለኝ ይህ ነው። እየፈለጉ መቀጠልን ማቆም ባይቻል በደረሱበት አለመብቃቃት ትልቅ ጉዳት ነው የደረስክበት ደግሞ 'አሁን' ነው ይህ ቅጽበት.አሁንና እዚህ።

አንድ ጊዜ የምረቃዬ መጽሔት ላይ ከፎቶ ስር ለሚሰፍር ጽሑፍ 'የእኔ ቀን ነገ ናት' የሚል ቃል ሰጥቼ ነበር... አሁን ላይ ቆም ብዬ ሳስብ 'ምን ሆኜ ነው ግን' እላለሁ. እንዴት ሰው እርግጠኛ ከሚሆንበት ዛሬ ይልቅ በማያውቀው ነገ ላይ የደስታውን ውበት ያንጠለጥላል?  ደስታ ኑረትን ግድ ይላል እኮ... 'ነገ እንትን ሳገኝ እደሰታለሁ' የምትል ከሆነ ለመደሰት ቀጠሮ እየሰጠህ ነው፣ ከዚያም በላይ ደስታህን በነገሩ መኖር አለመኖር ላይ እየመሰረትክ፣

ደግሞስ 'ለደስታ ምን ያህል ነው የሚበቃን?' ስንት ብር? ስንት መኪና? ምን ያህል ቁስ?

በዙሪያዬ ብዙ 'ያላቸው' - ተነጫናጮች እና ደግሞ 'ምንም የሌላቸው' ደስተኞች አየሁ ፣ ብዙ ሃብታም የበሽታ ቋቶችና ድሃ ፍልቅልቅ ፊቶችን ሳስተውልም ይሄ ጥያቄ ትዝ ይለኛል፦
.
.
መልሱ እኮ በአጭሩ "ደስታ ውስጣዊ እንጂ ቁሳዊ [ሰበባዊ] አይደለም" የሚለው ነው። ሆኖም በተግባባንበት መንገድ ሄጄ 'ለመደሰት ስንት ያስፈልገናል?' እላለሁ ፦ ምንም አይበቃንም!!* ምናልባት ምድርን የሚያህል ሃብት ቢኖረን እንኳ ሌላ ፕላኔት ማሰሳችን አይቀርም፣ ደስታ ግን ከብዛትም ሆነ ከነገር ጋር አትቆራኝም።

አዎን... ደስተኛ መሆን ካሻህ ባለህ ተብቃቃ Be Content እልሃለሁ!!

📍'የሰው ልጅ ፍላጎት ገደብ የለውም' በሚል ከንቱ ስብከት እየተነዱ 'ያለኝ ይበቃኛል' ማለት እንደሚከብድ ግልጽ ነው።ያም ሆኖ በፍላጎታችን ላይ የምንሰለጥን እንጂ ፍላጎት የሚሰለጥንብን እንዳልሆንን ማወቅም ጠቃሚ ይመስለኛል። አግበስባሽነት በማግኘት ላይ እንድትመሰጥ እንጂ ባለህ ደስታ እንድትፈጥር ፣ አሁን ያለህን ሐይወት እንድታጣጥም ዕድል አይሰጥምና።       

                     ደምስ ሰይፉ
                  @BridgeThoughts
    

            ውብ አሁን ❤️

@Ethiohumanity
@EthioHumanity

@EthiohumanityBot
🔴የሕይወት ግንድ ብዙ ቅርንጫፎች ነን!!

📍 አንድ ውቅያኖስ ላይ ነን  ‘የአንተ’ ታንኳ ሲናጥ ‘የእኔው’ ደንገል መንቀጥቀጥ ይጀምራል፣ ‘የእርሷ’ ጀልባ ሲቀዝፍ የባሕሩ ለመምቴ ይናጣል፣ የሰላምህ እርግብግቢት የሰላማችንን ንፋስ ይጠቅሳል… የሕመማችን ትንፋሽ የደስታ መንፈሷን ይበርዛል።ስለምን - ‘እኔም’፣ ‘አንተም’፣ ‘እርሷም’፣ ‘ሁላችንም' አንድ ነንና።

🔷መምህሩ ራማና ማሃርሺ …
“How are we Supposed to treat others?” ብለው ቢጠይቁት…
“There are no others” ሲል የመለሰው ለዚህ ነበር።

በተገበርከው ክፋት ብቻ ሳይሆን በተብሰልስሎትህ ሂደት ነገር ዓለማችን ይታወካል። በተነፈስከው በጎ ቃል አይደለም ባሰላሰልካት ደግነትም መውጣት መግባታችን ይዋባል… ብቻህን አይደለህምና የብቻ ሰላም የለህም… አልተነጣጠልንምና የብቻ ሕመምም አይኖርህም

የግዙፍ ውቅያኖስ አካል ነን ፣ እኛም ሆንን በዙሪያችን ያለው የተፈጥሮ ስንክሳር የውቅያኖሱ አንድ ጠብታ ነው ፣ አንዲት ጠብታ የምትፈጥረው ለመምቴ /Ripple/ የሌላውን ለመምቴ ትነካለች… እኒህ የሃሳብ፣ የስሜትና የድርጊት ለመምቴዎች በሌላኛው ተፈጥሮ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ አላቸው… በበጎም በክፉም… ተመልሰው ግን ወደ ምንጫቸው ይመጣሉ፣ በመዋኛ ገንዳ ውስጥ የፈጠርከው የውሃ ለመምቴ የገንዳውን ግድግዳ ገጭቶ ወዳንተ እንዲመለስ ማለት ነው።

🔶ከኔ ቤት ላይ የረጨኸው እሳት ከሆነ ነበልባሉ ያንተን ቤት ይነካል ፣ ሽቶ ስትረጨኝ የመዓዛው ቅንጣቶች ለአፍንጫህ ውብ ጠረን ይለግሳ፣ “You reap what you saw”ሰው የዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል ፣ ይህን ምስራቃውያኑ Karma ሲሉት ሌሎች ደግሞ Boomerang ይሉታል… Boomerang አውስትራሊያኖቹ አቦርጂኒስቶች ከእንጨት የሚሰሩት ደጋን ቅርጽ ያለው የአደን መሳሪያ ሲሆን ወርዋሪው ዘንድ ተመልሶ እንዲመጣ ተደርጎ የሚነደፍ ነው። ለሃሳብ፣ ለስሜትና ድርጊትህ መጠንቀቅ የሚኖርብህ ወላፈኑ ‘ለእኔም’፣ ‘ለእርሷም’፣ ‘ለእነርሱም’ እንደሚተርፍ በማሰብ ነው… ምክንያቱም
We are all One!

🔷ሰው ብቻ ሳይሆን ከዋክብቱ፣ ሕዋው፣ ምድሪቱ፣ እንስሳው… በሚታየውና በማይታየው ዓለም ያለው ነገር ሁሉ በአንዳች ተፈጥሯዊ ክር የተሳሰረ ነው… ማሰሪያው ስላልታየ መተሳሰሩ የለም አይባልም።

‘እዚያ ቤት ሲንኳኳ እኛ ቤት ይሰማል’ ‘ከወዲህ አንተን ሳማ እዚያ ከንፈር ትነክሳለህ’፣ ‘እከሊት ስታነሳኝ በስቅታዬ አውቀዋለሁ’፣ ‘የሰፈር ውሻ ሲያላዝን አንዱ አዛውንት ሊያልፉ ነው ማለት ነው’… ‘ውስጥህ ሲረባበሽ ራቅ ካለ ቤተሰብህ አልያም ወዳጅህ ቤት አንድ አደጋ አለ ማለት ነው’፣ 'ቅንድብህ ሲርገበገብ እንግዳ ሰው ልታይ ነው'፣ የጥንቶቹ ይሄ እውነት ስለገባቸው ይመስለኛል መሰል አባባሎች ያቆዩልን።

♦️በረከት በላይነህ "የመንፈስ ከፍታ" ላይ እንዲህ ይለናል👇

“የግልህ ወንዝ ስለሌለህ ብቻህን የምትሰራው ድልድይ የለም! የሰማዩ ርቀት፣ የምድሪቱ ስፋት በ’እኛ’ እንጂ በ’እኔ’ አይለካም፡፡ ውዱ ‘እኔ’ ከ’እኛ’ የተሰራው ነውና!”

🔷እዚህ ጋ ነው ስለ ዝምድናና ባዳነት ያለን ግንዛቤ መፈተሸ ያለበት፣ ስለ ዘርና ቀለም ያለን መረዳት መጤን ያለበት፣
Peter Russell “The Global brain” ብሎ ባሰናዳው ቪዲዮው ላይ አንድ በጨረቃ ላይ የተጓዘ የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ የተናገረውን ውብ ቃል ትሰማላችሁ
“When you are up there you are no longer an American citizen or a Russian citizen. Suddenly those boundaries disappear. You are a planetary citizen.”

🔑ኑረዲን ዒሳ በአንድ ግጥሙ.

“ባዳውን አፍቅሮ፣
ከባዳው ልጅ ፈጥሮ፣
እኔን ባዳዬ አለኝ - ሰባት ቤት ቆጥሮ፣
ልጁን ዘመዴ አለው - በፍቅር ታውሮ፡፡
ቅጠሉ ነኝና ለረጂሙ ሃረግ፣
እኔም ዘመዱ ሆንኩ - መቼስ ምን ይደረግ?” ብሏል…

❤️ፍቅር ሲገባን የልዩነት ቅዠት ይተናል ፣ ማንነት ሲገባን ሕብራችን ይታያል ፣ ጥበብ ሲያጥጠን ግን ልዩነት ያዜምልናል፣ ፍቅር ስንሰጥ በዙሪያችን ባሉት ላይ እርግብግቢቱ ፍቅርን ይወልዳል፣ክፉ ስናስብ ደግሞ በተቃራኒው ክፋት ይጠነሰሳል፣ከፊልዱ ውጭ እስካልሆንን ድረስ ከምላሹ ተጽዕኖ ልናመልጥ አንችልም።

                             ደምስ ሰይፉ
@bridgeThoughts
ውብ ቻናሉ ነው

         We are all One!
           ውብ ቅዳሜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
2024/06/24 04:23:04
Back to Top
HTML Embed Code: