Telegram Group Search
እነሆ የሰብዓዊ መብት አስደፋሪዎች: የትውልድን የዲሞክራሲ ተስፋ ቀባሪዎች: የፍትሕና የእኩልነት ጠላቶች--በአጠቃላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል አስቻዮች: ሴረኞች: አስፈፃሚዎችና ተባባሪዎች!!!!

ዛሬ ዓላማቸውን (እና በአብይ የተፈለጉበትን ፋሽስት የማንገስና ሕዝብ የማሳረድ ተግባር) ከፈፀሙ በኃላ: ወይ ከኃላፊነት ለመሸሽ: አሊያም በአብይ ፊት ጥቅም-ግልጋሎታቸውን ስለጨረሱ በመተፋታቸውና የታሪክ ቅርሻቶች በመሆናቸው--ሁሉም--ተራ በተራ ገለል ተደርገዋል:: ከተጠያቂነት ግን አያመልጡም::

እነዚህንና መሳዮቻቸውን ሁሉ ከያሉበት አድኖ ለፍርድ የሚያቀርብ ጠንካራ የሙያ በድን ተደራጅቶ ሥራ መጀመሩ ታሪክ የሚጠይቀው ግዴታ ነው::

#Genocidaires_to_ICC!
#Ethiopia_to_DenHaag!
#We_haunt_and_hunt_you!
ስለ ሥርዓቱ እብደት: ስለ ቀጣይ ሁኔታዎች: ስለ ሽግግር: ወዘተ... My discussions with Habtamu Tesfaye Gemechu on #KMN , 06/07/24

https://www.youtube.com/live/Lj8ive4qe_c?si=Vy91JuYENCM2i2IC
"አብይን ያካተተ የሽግግር ሂደት?"--ከምን ወደ ምን?
================================

ከአምባገነናዊ ሥርዓት: በተለይም ከፋሽስታዊ ዘር-አጥፊ ጦርነት በኃላ ለሚደረግ ሽግግር የሚወሰዱ እርምጃዎች ውስብስብና ፈርጀ-ብዙ መሆናቸውን ማንም ይረዳል::

በዚህ ዓይነት አውድ ውስጥ ተሁኖ: ለዘላቂ ሰላምና ለሁለንተናዊ የፖለቲካ መግባባት (comprehensive political settlement) የሚደረግ ድርድርና ውይይት: የራሱ ሂደት አለው::

ሂደቱም ቢያንስ ሶስት እርከኖች (steps) ይኖሩታል:: እነዚህን እርከኖች ለይቶ አለማወቅ: ወይም እርከኖቹን በመዝለል ቅደም ተከተላቸውን ማምታታት: ወይም ሶስቱንም በአንድ መጨፍለቅና እንደ አንድ ሁነት መቁጠር: የሚፈለገውን ሽግግር ለማምጣት እክል ይፈጥራልና: እያንዳንዳቸውን በዝርዝርና በጥልቀት ማየት ይገባል::

1) የመጀመሪያው እርከን: በታጣቂዎች መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት (Ceasefire Agreement) ላይ እንዲደርሱ የሚደረግበት ነው:: የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ የሚደረግ ውይይት: አፈሙዝ ለማዘጋት በሁለቱም ወገኖች የሚወሰዱ እርምጃዎችን ይመለከታል:: ተመልሶ ወደ መጠቃቃት እንደማይመለሱ መተማመኛ እርምጃዎችን ለይተው: ቅድመ-ሁኔታዎች (ካሏቸው) አስቀምጠው: እስካሁን ያገኙትን "ድል" ሳያስነኩ የቀሩ ድሎችን በሰላማዊ መንገድ እውን ለማድረግ የሚያስችል የጋራ ማዕቀፍ ያስቀምጣሉ:: ለዚህም ነው: አደራዳሪ (facilitator/mediator): ታዛቢ (observer): እና ዋስ (guarantor)የሚያስፈልገው::

በዚህ ሂደት የሚካተቱት ጭብጦች ከሞላ ጎደል የሚከተሉትን ያካትታሉ:-

ሀ)ተኩስ አቁሙ መች ይጀምራል እስከመቼ ይቆያል?

ለ)ማን ተቁስ አቁሙ በስምምነት መሠረት መፈፀም አለመፈፀሙን ይቆጣጠራል? አንዳቸው ስምምነቱን ቢተላለፉ: የጣሰው ወገን እንዴት ይታደባል?

ሐ)በሁለቱ ኃይሎች መካከል ስለሚኖረው ነፃ ቀጣና (buffer zone):

መ)ስለ ትጥቅ አፈታት ሂደት: ስለታጣቂዎች ቅነሳና ተሃድሶ: እንዲሁም ወደ ሰላማዊ ኑሮ መሸጋገር:

ሠ)ስለ ተያዙ:ስለ ታገቱና ስለ ታሰሩ ሰዎች መለቀቅ:

ረ)ለተጋላጭ ሰላማዊ ዜጎች ሊደርስስለሚገባ ሰብዓዊ እርዳታ:

ሰ)ወደ ቀደመው ሁኔታ (status quo ante) ለመመለስ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች:

ሸ)ስለ ተፈናቃዮች መመለስና መካስ: ስለ ምርኮኞች መለዋወጥ:

ቀ)ስለከተኩስ አቁሙ ሁኔታ መሳለጥ በኃላ ስለሚፈጠረው የጋራ የትብብር ተቋም (ማለትም የጊዜያዊ መንግሥት):

በ)በውጊያው ሂደት ለተፈፀሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት ስለሚሰጥ ዋስትናና ስለሚወሰዱ አስተማማኝና ተጨባጭ እርምጃዎች: (በፊት ተጥለው የነበሩ ውንጀላዎች ስለሚነሱበት ሁኔታ) ወዘተ እና

ሌሎች ተዛማጅ ጭብጦችን ይመለከታል::

ይሄ ስምምነት የሽግግር ሥምምነት ሳይሆን:በዋናነት: መገዳደልን ማቆምን የሚመለከት ነው:: በሁለቱ ወገኖች የሚፈፀሙ የኃይል ተግባራትን የማክሰም ሂደት ነው::

ይህ ሂደት በስኬት የሚገባደድ ከሆነም: ከዚህ የግጭት/ጦርነትና ፖለቲካዊ ክፋት (political evil) ሁኔታ በማያዳግም ለመውጣት መስማማትካለ: ይሄን ለማድረግ የሚያስችል የሽግግር ሂደት ማዕቀፍ (Framework for Transitional Process) ማስቀመጥ ይቻላል:: ይሄንን የሚያመቻች ጊዜያዊ የጋራ መድረክ (በኢትዮጵያ ሁታ ደግሞ: ታጣቂዎቹን ያካተተ አገራዊ ጊዜያዊ መንግሥት) እንዲኖር እስከመስማማት ሊደርስ ይችላል::

2) ሁለተኛው እርከን: የጋራ መድረኩን (ጊዜያዊ መንግሥቱን) ለማቋቋምና በሚቋቋመው ጊዜያዊ መድረክ/ መንግሥት ውስጥ ተዋጊ ወገኖች ያላቸውን የሥራ ድርሻ: መብት: ሥልጣንና ኃላፊነት: የመድረኩ/መንግሥቱ (ውሱን) ኃላፊነት(mandate): የሥራ ጊዜ ላይ ውይይት ተደርጎ ስምምነት የሚደረስበት ነው::

ይህ ሂደት ውጤታማ ከሆነ: በስምምነቱ መሠረት ጊዜያዊ መድረኩ/መንግሥቱ ወደ ሥራ የሚገባበት እርከንነው::ይህ ሁለተኛ እርከን የሽግግር ሂደት: ሙሉ የፖለቲካ መግባባት ለመፍጠር ጥረት የሚደረግበት ሳይሆን: ተኩስ አቁሙን መተግበርና ከአለፈው የጦርነትና የፖለቲካ ክፋት ለመላቀቅ የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች የሚደረጉበት (ማለትም: ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት መፍጠር: እስረኞችን መፍታት: የታገዱና የተሰደዱ የፖለቲካ ኃይሎችን መመለስ:ድንበርን መዝጋት: የወንጀል ተጠርጣሪዎችን በሕግቁጥትር ሥር ማዋል: ለዕለትተለት ኑሮ የሚያስፈልጉ የአስተዳደርና የግልጋሎቶች ፍሰትን ማሳለጥ: ቁልፍ ለሆኑ አገራዊና ማህበራዊ የመሠረተ-ልማት አውታሮች አስፈላጊውን የጥበቃ ሽፋን መስጠት: እና የመሳሰሉት የሚፈፀሙበት) እርከንነው::

በተጨማሪም: ወደ እውነተኛ ሽግግር ለመሄድ የሚያስችሉ የዝግጅት እርምጃዎች የሚወሰድበት ወቅት ነው:: ለዚህ የሚያስፈልገው ሁሉን አካታች የሆነ የሽግግር ጉባኤ ለማካሄድ እንዲቻል ለሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጥሪ የሚደረግበት: ሁሉም ኃይሎች ለመሳተፍ እንዳይችሉ የተቀመጡ ህጋዊና ህጋዊ ያልሆኑ ገደቦች ሁሉ የሚነሱበት: መሠረታዊ የሲቪክና የፖለቲካ መብቶች (በተለይ: የማሰብ: እራስን የመግለፅ: የመናገር: የመፃፍ: የመሰብሰብ: እና የመደራጀት: መብቶች) ያለ ገደብ የሚከበሩበት: የውይይት አጀንዳ የሚለይበት (ቅድመ-ፖለቲካዊና ፖለቲካዊ የሆኑት ተነቅሰው የሚወጡበት): ለመፍትሄ እርምጃዎች ምክንያታዊ የጊዜ ተመን (ሰሌዳ የሚቀመጥበት): ወዘተ ወቅት ነው::

ይህ ሂደት: አገራዊ የሽግግር ጉባኤ ተካሂዶ: የሽግግር መንግሥት ሲቋቋምና ጊዜያዊዉ የጋራ መድረክ (ወይም ጊዜያዊው መንግሥት) ኃላፊነቱን ለሽግግር መንግሥቱ ሲያስረክብና እራሱን ሲያከስም ይጠናቀቃል:: በዚህም: ወደ ሶስተኛውና የመጨረሻው የሽግግር እርከን ለመሄድ እድል ይፈጠራል::

በዚህ በሁለተኛው እርከን በተባባሪነት ሲሳተፍ የቆየው ነባሩና የፖለቲካ ክፋትን ሲተገብር የነበረው የአገሪቱ ቡድን(ፈቃደኛ ሆኖ ከተሳተፈ) ጉዞውን እዚህ ጋ ገትቶ ከፖለቲካው ሂደት እራሱን ያገልላል: ወይም እንዲያገልል ይገደዳል:: (ይሄን በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለሁ::)

3) ሶስተኛው እርከን: የሽግግር መንግሥት ተቋቁሞ: አገሪቱን ወደ ሰላማዊና የተደላደለ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመምራት የሚንቀሳቀስበት ነው:: የሽግግር መንግሥቱ: ባለፈው የጦርነት: የዘር ማጥፋትና የፖለቲካ ክፋት ዘመንና ወደፊት ሊመጣ ባለው የእፎይታ: የፍትሕና የዴሞክራሲ ዘመን መካከል የሚሆን አገናኝ ድልድይ ነው:: የዴሞክራሲ አዋላጅ ነው::

በዋናነት የዚህ (የሽግግር) መንግሥት ኃላፊነት (mandate): በዋናነት የሚከተሉትን የሚመለከት ይሆናል:-

ሀ) ሰላምን መጠበቅ:

ለ) አንገብጋቢ ለሆኑ ችግሮች ወቅታዊ ምላሽ መስጠት:

ሐ) ዴሞክራሲያዊ አካታችነትንና ተሳትፎን ለማሳለጥ የሚያግዙ ህጎችንና ደንቦችን ማውጣት: ፖሊሲዎችን መቅረፅ: ለዚህ የሚሆኑ እርምጃዎችንም መውሰድ:

መ)ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግና ተጠቂዎችን ለመካስ የሚያስችል የሽግግር ፍትህ ህግ/ፖሊሲ ማእቀፍ ማውጣትና ዓለማቀፋዊ መስፈርትን የሚያሟሉ የሽግግር ፍትህ ተቋማትን ማቋቋም:

ሠ) ሰብዓዊ እርዳታ ለተጎጂዎች ማቅረብ: ተፈናቃዮችን መመለስ:

ረ) ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚጠቅሙ የፀጥታ (የደህንነት: የመከላከያ: የፖሊስ): የሚድያ: ሲቪል ማህበረሰብ: የምርጫ ቦርድ: የፍትህ: ወዘተ ማሻሻያ ፖሊሲዎችን መንደፍና መተግበር:
ሰ) ለከራረሙ: ለአደሩና ለተወሳሰቡ ቅድመ-ፖለቲካዊ የፍትሕ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ: በሕዝቦች ዘንድ መተማመንን የሚያጠነክሩ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን (ለምሳሌ ሕዝበ-ውሳኔ) ከነ ጊዜ ሰሌዳው ማስቀመጥና ተቋማዊ ዝግጅት ማድረግ::
---
እነዚህን እርከኖች በመቀላቀል: ቅደም-ተከተላችውን በማምታታት: ወይም በአንድ ጨፍልቆ "የሽግግር መንግሥት/ የባላደራ መንግሥት" እያሉ ችግሩንና መፍትሔውን ማቀላቀል--ከዚህም ፍሬያማ ውጤት መጠበቅ--አይቻልም::

--

አሁን ባለው ሁኔታ: ብልፅግናን "የሽግግሩ አካል እናድርግ" ማለት: የአብይን የስልጣን ዘመን በማራዘም: የችግሩን እድሜ ማስቀጠል ነው እንጂ ሽግግርን ማማጣት አይደለም::

ብልጥግና ሙሉ በሙሉ በኃይል እንዳይወገድ ከፈለገና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መጨረስ ከፈለገ: የተኩስ አቁም ድርድሮችን በመጀመር: አፈሙዝ ለማዘጋት በሚደረግ ሂደት (የሽግግር የመጀመሪያ እርከን ሂደት ላይ) ሊሳተፍ ይችላል::

የተኩስ አቁም አድርጎ: የእሱ አካሄድ ስህተት መሆኑን ተቀብሎ: ወደዴሞክራሲ የሚደረግ ጉዞ ይሻላል የሚለውን ከተቀበለና እራሱንም ለማክሰም--ለአንዳንድ ባለስልጣናቱም ምህረትና ይቅርታን ተደራድሮ--ከተስማማ ደግሞ: የጊዜያዊ መንግሥት ረዳት አካል (junior partner) ሆኖ: የሽግግር መንግስት እስኪቋቋም ባለው ጊዜያዊ የጋራ መድረክ ወይም በጊዜያዊ መንግሥት መሳተፍ ይችላል:: በዚህ ሂደቱ ሁለተኛ እርከን ላይ ተሳታፊ ይሆናል ማለት ነው::

ከዚህ በኃላ ግን ወንጀለኞቹን ለፍትህ አካላት አስረክቦ: እራሱን አክስሞ መቀመጥ እንጂ የሽግግር መንግስቱ አካል ሊሆን አይችልም:: ብልጥግና አብሮን ከተሻገረማ አገሪቷስ ከእርሱ መች ልትሻገር ነው?

አብይን የመፍትሔው አካል አድርጉ የሚለው የልጆች ጨዋታ: የአብይን ፋሽስት መንግሥት በመጠኑ liberalise አድርገን: ሌሎች ኃይሎችንም ጨምረን: ወደ ፊት እንቀጥል እንደማለት ነው::

ፋሽስት liberalise አይደረግም:: በታሪክ እንደታየው: Liberalismን ቀርጥፎ ውጦ ብቻውን ይቀጥላል እንጂ::

ይሄን ብልጥግናን liberalise የማድረግ ጥሪ የአሜሪካ እንደሚሆንይገመታል:: አብይየእነሱ መንግሥት ስለሆነ (ምናልባትም በእነሱ ዓይን ሊብራል ዴሞክራት ስለሆነ) ሰላምን በመዋዋልና ሌሎችን በማካተት የበረታና የጠነከረ እንዲሆን የመፈለግ ዝንባሌ ሊኖራቸው ይችላል::

የኢትዮ-አማራ ልሂቃን የፖለቲካ ኃይሎች "አብይ የሌለበት ሽግግር አይኑር" ማለታቸው የሚያሳየው: በመሠረቱ የአብይ መንግሥት: እነሱ ለኢትዮጵያ ተመራጭ ነው የሚሉት መንግሥት መሆኑን (እና በጉዞው መኃል ላይ ትንሽ ከመስመር የወጣባቸው በመሆኑ: ትንሽ መስተካከል እንዳለበት እንደሚያምኑ) ነው:: አብይ በመሠረቱ የእነዚህ የኢትዮአማራ ልሂቃን መንግስት መሆኑን ግልፅ ያደረገ ሂደት ነው:: (ቀደም ብለው ያለ ገደብ ለአብይ ሲያሸበሸቡ የነበረ መሆኑን ልብ ይሏል:: ሰፊ የዘር ማጥፋት ሲይካሄድ ጭምር ድጋፋቸውን እንዳልነሱት ማስታወስ ያስፈልጋል::

ምክንያታቸው ከላይ ያልነው ካልሆነ ግን: ሌላ ሃሳብ--ከአብይ የተሻለ መፍትሔም--እንደሌላቸው በግልፅ ያሳያል:: የተሻለች ኢትዮጵያን ማየት ሲፈልጉ: ለማየት የሚችሉት: አብይ ያየውን ያህል ብቻ መሆኑን ያሳያል:: And that is tragic. All too familiar to us, but tragic nonetheless.

(ይቀጥላል)
Forwarded from KMN
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Godina Salaalee Aanaa Dharraa
Gochaa Sukkanneessaa ebla(12/8/2016 )Shawaa Kaabaa Aanaa Darraatti Iddoo Kaarra Orogooo Jedhamtutti warrani sirna pp ummata oromoo irraatti Gochaa sukkaaneessa rawaachaa jira qoote e bullaa Nagahaa Sheneedh jeechuun harkaa Dukaatti hidhuun mana hidhaatti bassaanii Raashaanan

Ajjeechaan sukkaaneesan torbee kaan keessa ta'e Darraati hedu u namaa gadisissaa.

Maqaan isani
1 seexiyee asheetu fi
2 sayidee Abooyyee yeroo isaan Rashanaman😢
ነፍጠኛን እንጠላለን: እንታገለዋለን: እነቅለዋለን: መልሶ እንዳይበቅል አድርገን እንቀብረዋለንም!!!
==============
(10 July 2023 ተፅፎ: አሁን በድጋሚ የተፖሰተ)

የነፍጠኛ-ገባር ሥርዓት ሲወቀስ: ነፍጠኛ ሲነቀፍ የሚከፋህ ከሆነ: ወይ እራስህ ከታሪክ ፍሰት ያፈነገጥክ: anachronistic የሆንክ) ነፍጠኛ ነህ: ወይ ነፍጠኛ ለመሆን እየጎመዠህ ነው: ወይም ደግሞ የነፍጠኞችና የነፍጠኛ ገባር ሥርዓት ናፋቂና አዛኝ (sympathiser) ነህ::

ነፍጠኛ: ነፍጠኝነትና: የነፍጠኞች ሥርዓት መጠላታቸው የሚያንገበግብህ ከሆነ: ኢፍትሃዊነትንና ታሪካዊ ግፍን ለማስቀጠል ትሻለህ ማለትነው::

ያም ሆነ ይህ: እራስህን ታሪካዊ ግፍ (historical injustice) ከፈጸመ ሥርዓትና ከአስፈጸሙ ግለሰቦች ጋር በማቧደን የታሪካዊው ግፍ ባለቤት ሆነሃል ማለት ነው::

ነፍጠኝነትን የራስህ ካደረግክ: ሃላፊነቱንም ትሸከማለህ:: ዛሬም በነፍጠኝነት ልቀጥል ካልክ: የወትሮው ተቋቁሞ (resistance) ይነሳብሃል: ይታገልሃል: በመጨረሻም ያሸንፍሃል: ለፍርድም ያቀርብሃል::

የነፍጠኞችን ወንጀልና የግፍ ተግባር እንዳይጋለጥ ለማድረግ ቃሉን እንኳን እንዳንጠቀም ለማሸማቀቅ መሞከር: ግፍ አድራጊውን (ወራሪ: ነጣቂና ዘር-አጥፊውን) በሥሙ አትጥሩት ማለት ነው::

ይሄ ደግሞ ግፈኛን ማጽደቅና ልዩ ቦታ (privilege) እንዲሰጠው ማድረግ ነው::

ነውረኛውን ለማጽደቅ ሲባል ብቻ: ነውሩን የምናጋልጠውንና የምናስታውሳችሁን እኛን "ነፍጠኛ" የሚለውን ቃል መጠቀም "የጥላቻ ንግግር አደረጋችሁ" ማለት ደግሞ ጥላቻንም ሆነ የሚጠላውን (መጠላት ያለበትን) ለይቶ አለማወቅ (ወይም አውቆ አለማወቅ--strategic ignorance) ነው::

እንደ ሰው የሚያስብ ጭንቅላት ቢኖርህ ኖሮ: "ነፍጠኛ አይነቀፍ": ወይም "እኔነፍጠኛ ነኝ" ብሎ መፎከር: ተጠቂዎቹን ኢላማ ያደረግ የጥላቻ ንግግር መሆኑን ታስተውል ነበር:: ይሄም የግፉን ተጠቂዎች መልሶ የሚያጠቃ (re-victimise የሚያደርግ): አሁን እያጠቃ ያለ የጥላቻ ንግግር (active hate speech) መሆኑንም ታስተውል ነበር:: እንደ ሕዝብም--እንደ ፖለቲካ ማሕበረሰብም--ነፍጠኛ: ነፍጠኝነትና ሥርዓቱ በታሪካችን ውስጥ መከሰቱን እራሱ ታፍርበት:ታዝንበትና ይቅርታ ትጠይቅበት ነበር:: ግፉንም ለመሻር የተለያዩ የፍትህና የእርምት እርምጃዎች ትወስድና ታስወስድ ነበር::

ይብሱኑ: የሆነውን በመካድ: አገሩም አገር እንዳይሆን: ሕዝቡም ሕዝብ እንዳይሆን: ለፍትህ የቀና የፖለቲካ ማሕበረሰብ ሆኖም እንዳይሠራ የማያባራ የሚዲያ ጫጫታ በመፍጠር: ግፉ እንዳይነሳ/እንዳይታወስ "የጥላቻ ንግግር ነው" እያልክ ትውልዱን ለማፈን ትራኮታለህ::

ይብላኝልህ ላንተ ከራስህም ጋር እንዴት እንደምትኖር ላላወቅከው እንጂ "ሌሎቹ" ሕዝቦችስ ከቆረጡና ከተቆረጡ ቆዩ::

ጥላቻችሁንም ንግግራችሁንም እዛው ለራሳችሁ አጉተምትሙ::

ታሪክንና የትውልዶችን ሃቅ መታገል እንቀጥል ካላችሁ: መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ::

ነፍጠኞችን: ነፍጠኝነትንና ማናቸውንም የነፍጠኛ ሥርዓት መገለጫ የሆኑ እሴቶችን በትግላችን ከምድራችን ላይ እንነቅላለን: እንቀብረዋለንም!!!

#suit_yourself_if_you_are_a_nafxanyaa!
Our struggle has not been to “liberalise” and sanitize #AbiyAhmed’s regime by making it “inclusive”. That’s why the call for collaborating with his regime (even in the name of “peace”) is a non-starter. You cannot liberalize a genocidal fascist regime. Being “included” in such a regime is inhabiting the underbelly of totalitarianism leaving the marginal space for resistance outside of it. In the end, “inclusion” becomes obliteration of the peripheral space of resistance.
#AbihAhmed_is_a_genocidaire! #No_Transition__WITH_PP!
#PP_to_ICC #Ethiopia_to_DenHaag
ሽግግር በክልሎች ብቻ? ሕገወጥ የሥልጣን ክፍፍል: ሽግግር ሳይሆን ጉቦ (ወይም co-optation) ነው
=================
የፌደራል መንግሥቱን ያላላካተተ: በክልሎች ብቻ የሚዋቀር የሽግግር ሥርዓት የለም: አይኖርምም! ካለም የቤት-የለሽ ልሂቃን ልብ ውስጥ ተጠንስሶ እዚያው የሚሞት/የሞተ ጭንጋፍ ሃሳብ ነው!

የፌደራል መንግሥቱን የማይመለከትና በክልሎች (ለዚያውም በትግራይ: በአማራ: በኦሮሚያ እና በከፊል ሶማሊ ውስጥ ብቻ) የሚዋቀር የሽግግር ሥርዓት ምን የሚሉት ነው?

ዋናውን ችግር ፌዴራል ላይ አስቀምጦ: በክልል የሽግግር መንግሥት ማቋቋም ይገባል የሚሉ "መካሪዎች" ግን ክልሎቹን ብቻ ለይተው የሚያሸጋግሩት ከምን ወደምን ነው?

ለመሆኑ የሽግግር ጥያቄ ያለው ሕዝብ የእነዚህ የተጠቀሱ ክልሎች ሕዝብ ብቻ ነው? ክልሎቹን እያመሰና በዚያም ችግር እየፈጠረ ያለውስ የፌደራሉ መንግሥት አይደለምን?

የፌደራል መንግሥቱ ሳይሻገር ክልሎቹ ወደ ምንድነው ሚሻገሩት?

ዘር-አጥፊው የፌደራሉ መንግሥት ችግር ስለሌለበት ነው ሽግግር ማያስፈልገው? ለመሆኑ ሽግግር ማለት የክልል መንግሥት ሥልጣንን ከብልፅግና ጋር መከፋፈል ነው ብሎ ያስተማራቸው ማንነው?

የቤት-የለሽ ኢትዮ-ልሂቃን: አንዳንድ የኦሮሞ የሥልጣን ተስፈኞች: እና ከብልጥግና ጋር በአዲስ መልክ ለመጠጋጋት የፈለጉ ኩርፈኛ የነበሩ ኦሕዴዶች: የሽግግር መንግሥት እሳቤያቸው ይሄ መሆኑ ነው:: ("ክልል ላይ እናተኩር" የሚሉ ቆየት ያሉ ጫጫታዎች አሁን "የሽግግር ሃሳብ" ተብለው "በአዲስ መልክ" መቅረባቸው ነው::

ገና ለገና የብልጥግና ተቃዋሚዎች አብይን ከጣሉት ክልሎች ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣንና መብታቸውን ይጠቀማሉ: ብለው ከመስጋት የተነሳ--የብሔሮችን/የክልሎችን ሉዓላዊ መብትተከብሮ ከማየት ሞታቸውን ስለሚመርጡ--ከወዲሁ ክልሎቹ ውስጥ እየታየ ያለውን ተቃውሞ ለማስተንፈስ እና ለመግታት (contain ለማድረግ) ሲባል: በሽግግር ሥም: በክልል ያለ የሥልጣን ፍርፋሪ ለማደል ዘዴ መዘየዳቸው መሆኑነው::

They hate the nations so much that they are willing to cooperate with a genocidal regime. ለነገሩ እነሱም ሥልጣን አልያዙም እንጂ: ከዚህ ተግባር መች አርፈው ያውቃሉ? ቀድሞስ ቢሆን አብይ የጋለበው የዘር ማጥፋት ጋኔን የእነሱ አልነበር? በጦርነቶቹስ ሁሉ "ግፋ በለው" ሲሉ አልነበር? አሁን አቅም ሲያንሰው ሸርተት አሉ እንጂ?

የሆነ ሆኖ: ይሄንን የእነሱ የሽግግር ሃሳብ የነፍስ-አባታቸው የአሜሪካ መንግሥት ይገዛውና ያስተገብረው እንደሆን አብረን የምናየው ይሆናል::

ምኞት አይከለከልም:: ይሄን የፈለጉትን ውጤት ለመግለፅ ግን "ሽግግር" የሚለውን ቃልና ጽንሰ-ሃሳብ በመጠቀም የሚፈለገውን እውነተኛ የሽግግር ሥርዓት ሂደት አያምክኑብን::

#ብኩን_ልሂቅ_ከንቱ_ቅዠት!
#አለማወቃቸው_ሳያንስ_ማምታታቸው!
This is how #AbiyAhmed’s soldiers raze villages to the ground under the pretext of fighting #OLA. This is how they execute their project of “draining the ocean in order to exterminate the fish.” An episode of burning down residential villages in Gujii Zone., Oromia.

https://www.facebook.com/share/v/dSSLkh6DEWJnaTrh/?mibextid=WC7FNe
Discussion with #KMN on:

1) Abiy’s destruction of villages in Gujii Zone;

2) Hostage-taking as #AbiyAhmed’s new political currency; and

3)Transition constitutionally or extra-constitutionally? Through (constitutional) care taker government, or victors’ provisional government leading to a Transitional Government, or a Transition through the National Dialogue Commission??? Clarifying the concepts…
https://www.youtube.com/live/xkDR9MDJ8yI?si=z7Z4V1nP-e_YZcDj
2024/07/17 03:01:44
Back to Top
HTML Embed Code: